በዩናይትድ ስቴትስ የሚደገፉት የሶርያ ዲሞክራስያዊ ኃይሎች እስላማዊ መንግሥት ነኝ በሚለው ፅንፈኛ የአማፅያን ቡድን ተይዘው የነበሩ 41 ቦታዎችን አስመልሰናል አሉ።
በዩናይትድ ስቴትስ የሚደገፉት የሶርያ ዲሞክራስያዊ ኃይሎች እስላማዊ መንግሥት ነኝ በሚለው ፅንፈኛ የአማፅያን ቡድን ተይዘው የነበሩ 41 ቦታዎችን አስመልሰናል አሉ። እስላማዊ መንግሥት ነኝ የሚለው ቡድን ከሚቆጣጠረው የመጨረሻ ምሽግ ለማባረር እየተዋጉ መሆናቸው ታውቋል።
"ሙስጣፋ ባሊ" የተባለው የሶርያ ዲሞክራስያዊ ኃይሎች ቃል-አቀባይ ባግሁዝ በተባለው መንደር የነበረውን የጽንፈኛው ቡድን ምሽግን አፍርሰናል ሲል በትዊተር አስታውቋል። ይሁንና ከባድ ውጎያ መቀጠሉን ሳይገልፁ አላለፈም።