ሰሞኑን አዲስ አበባ ውስጥ ተካሂዶ የነበረው የሰላም ድርድር ውጤት ሊያመጣ ይችላል ተብሎ ተገምቶ የነበረ ቢሆንም ፣ የመንግስት ሀይሎች ቤንቲዩ እየተባለች የምትጠራውን የነዳጅ ዘይት የሚገኝበትን ቦታ ለመቆጣጠር ጥቃት መጀመራቸው በሰላም ስምምነቱ ላይ ያለው ተስፋ እንዲጨልም አድርጎታል።
በቤንቲዩ የሚደረገውን ጦርነት በመሸሽ በርካታ ስደተኞች አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል። እስካሁን ድረስ ከ1 ሺ ያላነሱ ዜጎች በግጭቱ ተገድለዋል። በመቶሺዎች የሚቆጠሩ የአገሪቱ ዜጎችም አካባቢያቸውን ለቀው ተሰደዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎቹን ከደቡብ ሰዳን ለማስወጣት እንቅስቃሴ አልጀመረም።
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar