ከወቅታዊ የአገራችን ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስአበባ ከስድስት ኪሎ እስከድላችን ሐውልት ድረስ ሕዝባዊ ሰልፍ ለማካሄድ ግንባሩ መርሃግብር ነድፎ የተንቀሳቀሰ ቢሆንም የአዲስአበባ ከተማ አስተዳዳር ከተማዋ በተለያዩ ልማቶች የተቆፋፈረች በመሆኑዋ ሰልፉን ለማካሄድ አመቺ አይደለም በሚል ምክንያት ፈቃድ መከልከሉ ታውቋል፡፡መድረክ የአደባባይ ሰልፉን በቤት ውስጥ ስብሰባ በመቀየር በድጋሚ ለአስተዳደሩ እንዲያውቀው ያስገባው ይፋዊ ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ አግኝቶ ስብሰባው በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አካባቢ በሚገኘው የመብራት ኃይል አዳራሽ ሐምሌ 28 ቀን 2005 ለማካሄድ ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ታውቋል፡፡
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar