ችግሩ የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች ሀላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣታቸውና ነዳጁን ማከፋፈል በማቆማቸው የተፈጠረ ነው በማለት የንግድ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
የኦይል ሊቢያ 48 ያህል ተሽከርካሪዎች ወደ ሌሎች ኩባንያዎች በመሄዳቸው ፤ የነዳጅ አቅርቦት እጥረቱ ከተሽከርካሪ እጥረት ጋር ተያይዞ መምጣቱንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ሚኒስትሩ ” የአንዳንድ የነዳጅ ኩባንያዎች ድርጊት በትራንስፖርት እንቅስቃሴው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ከመፍጠር በዘለለ ክፍለ ኢኮኖሚውን በእጅጉ የሚጎዳ በመሆኑ ፤ ይህን ድርጊት በሚፈፅሙ ኩባንያዎች ላይ አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ መንግስት ለመውሰድ እንደሚገደድ” ገልጸዋል። አከፋፋዮች በበኩላቸው ምንም አይነት ነዳጅ እንዳልቀረበላቸው እየገለጹ ነው።
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar