ኢሳት ከወር በፊት ዜናውን ይፋ ባደረገበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ መንግስት የሱዳን ኢምባሲ የዲያስፖራ ዘርፍ ሃላፊ ሆኑት አቶ….ወጣቱዋ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ ገልጸው ነበር።
ይሁን እንጅ ጋርዲያን እንደሚለው ፣ ወጣቱ የ3 ወር ነፍሰጡር እያለች በ7 ጎረምሶች መደፈሩዋን ወዲያውኑ ለፖሊስ ብታመለክትም፣ ፖሊስ ግን የኢድ አል ፈጥርን በአል ሰበብ በማድረግ አቤቱታዋን ሳይቀበላት ቀርቷል።
ወጣቱዋ ዝሙት አለመፈጸሙዋንና ተገዳ መደፈሩዋን ብትናገርም ተሰሚነት አላገኘችም። የሱዳን ፍርድ ቤት የአገሪቱን ፖሊስ ገጽታ ለመጠበቅ ሲል እንዲሁም ጥፋተኞችም ለመታደግ ሲባል ንጹዋን ወንጀለኛ አድርጎ ማቅረቡ አሳሳቢ መሆኑን ሲሃ መግለጹን ዘጋርድያን ዘግቧል።
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar