ይህ የአንድነት ፓርቲ አዲስ አበባ ምክር ቤት የሚጠራዉ ሰልፍ፣ የአንድነት ፓርቲ ይፋ ካደረገው የአሥራ አራት ከተሞች የሚሊየንም እንቅስቃሴ የተለየና በተጨማሪ የሚደረግ ሲሆን፣ የሚሊየነም እንቅስቃሴ በመሬት ባለቤትነትና በፍትህ ላይ ያተኮረ እንደሆነ በስፋት የተዘገበ ነው።
የአዲስ አባበ የአንድነት ምክር ቤት፣ በሃያ ሶስቱም የአዲስ አበባ ወረዳዎች መቃቅር ያለው ሲሆን፣ ከማእከላዊ ፓርቲ ዉጭ፣ በራሱ በርካታ እንቅስቃሴዎች የሚያደርግ ምክር ቤት እንደሆነ ይታወቃል። ፓርቲዉ አባላትን በአዲስ አበባ እንዳደረጉት በራሳቸው አነሳሽነት ሰላማዊን ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንዲያደርጉ የሚያበረታታ እንደሆነ ብዙ ጊዜ አመራር አባላቱ ሲናገሩ ተሰምተዋል።
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar