fredag 6. juli 2018

ሰበር ዜና….ብጹዕ አቡነ ማቲያስ ስልጣናቸውን በሚቀጥሉት ሳምንታት በፈቃዳቸው ሊለቁ ነው

ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ እና ዶ/ር ደብረጽዮን
ባለፈው ሳምንት ሲካሄድ የነበረውና ለአራት ቀናት ያክል የተካሄደው  36ኛውየሰበካ  መንፈሳዊ  ጉባዔ   ላይ ከሌሎች ጳጳሳትና ከቤተክህነት አስተዳደር ጋር በአደባባይ እስጥ አገባ ውስጥ ያሳለፉት አቡነ ማትያስ በጉባዔው ጣልቃ ስልጣናቸውን ለመልቀቅ እንደሚፈልጉ ለቅርብ ሰዎቻቸው ተናግረዋል። በቤተክህነቱ አካባቢ ስልጣናቸውን የሚገዳደሩና የማይታዘዟቸው እየበዙ በመምጣታቸው ክፉኛ የተበሳጩት አቡነ ማቲያስ በመጪው ጊዜ በሚጀምረው የሲኖዶሱ ጉባዔ ላይ መልቀቂያ ማቅረብ እፈልጋለሁ ብለዋል። የፓትርያርኩ እርምጃ ያሳሰበው መንግሥት ፓትርያርኩ ሀገሪቱ ያለችበትን አስቸጋሪ ሁኔታ አጢነው ስልጣን ከመልቀቅ ይልቅ በውይይት ችግሮችን እንዲፈቱ ከማክሰኞ  ምሽት  ጀምሮ አንድ ቡድን በመላክ እያግባባቸው ነው።
አቡነ ማትያስ የቤተክርስቲያኒቱ የወንጌል ማስፋፋትና ትምህርት አንድ አሀድ ከሆነው ማኀበረ ቅዱሳን ጋር የተካረረ ውዝግብ ውስጥ  የቆዩ ሲሆን መንግሥት ማኅበሩን እንዲዘጋው  እስከመጠየቅ ደርሰዋል። ማኀበሩ በቅርቡ የጀመረውን የቴሌቭዥን ስርጭትም   ህገወጥ  በመሆኑ ሊታገድ ይገባል ባይ ናቸው አቡነ ማትያስ።  ፓትርያርኩ  ለአራት ቀናት  በተካሄደው    የመንፈሳዊ ሰበካ ጉባዔ ላይ የማኅበረ ቅዱሳን ተወካዮች እንዳይካፈሉ ትዕዛዝ ሰጥተው ማኅበሩን እንዳይሳተፍ ማድረግ ቢችሉም የቤተክህነት አስተዳደርና ሌሎች ገዳማት የማኅበረ   ቅዱሳንን   ሚና የሚያጎላና የሚያወድስ ሪፖርት ማቅረባቸው አቡነ ማትያስን አስከፍቷቸዋል።
ጉባዔው ማኅበረ ቅዱሳንን ከማውገዝ ይልቅ ለቤተክርስቲያኒቷ አለኝታ የሆነና ድጋፍ  ሊደረግለት  የሚገባ መሆኑንም የተናገሩ አባቶች ነበሩ። በአራቱ ቀን ጉባዔ ከአቡነ ፋኑኤል ጋር የከፋ የቃላት  ልውውጥ ያደረጉት ፓትርያርኩ ብዙውን ጊዜ በዝምታና በማኩረፍ እንዳሳለፉ ከጉባዔው ተሳታፊዎች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የውዝግቡን  መካረር  ተከትሎ መንግሥት የጉባዔውን ሂደት በቅርብ ሲከታተል የቆየ ሲሆን በማጠቃለያ የአቋም መግለጫ ላይ የማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቭዥን ስርጭት “ህገ- ወጥ” መሆኑን የሚገልፅ አንቀፅ ከጉባዔተኛው ስምምነት ውጪ እንዲጨመር መደረጉ ብዙዎችን አሳዝኗል። አንቀፁ የተጨመረው አቡነ ማትያስን “ተሰሚ” አድርጎ ለመሳል “በትዕዛዝ” የተካተተ እንደሆነ ከቃለጉባዔ መዝጋቢዎች ተሰምቷል።
አቡነ ማትያስ
ምንጭ አንድነት ጋዜጣ

ነፃነት ተጎናፅፈናል የብልፅግና ጉዞም ተጀምሯል ለወጡን እንጠብቅ! (ታዬ ደንዳዓ

ለኢትዮጵያ ህዝብ
ለወጡን እንጠብቅ! (ታዬ ደንዳዓ)
እንደ ህዝብ እና እንደ ሀገር ፍላጎታችን ነፃነት እና ብልፅግና ነዉ። ይህ ያልተሳካልን በእርግማን ሳይሆን ከጅቦች አገዛዝ ራሳችንን ማላቀቅ ባለመቻላችን ነዉ። አሁን ነፃነት ተጎናፅፈናል። የብልፅግና ጉዞም ተጀምሯል። ክብር እና ዕድሜ ለዶር አብይ እና ለጓዶቻቸዉ! በሦስት ወር ጊዜ ዉስጥ በጣም ብዙ ለዉጥ አይተናል። በዝህ ፍጥነት በሁለት እና ሦስት ዓመታት በሀገራችን መሠረት ያለዉ ሠላም፣ ዴሞክረሲ እና ልማት ይገነባል። ለዝህ ላበቁን ቄሮዎች፣ ፋኖዎች እና ዘርማዎች ክብር ይገባል።
ጅቦች ግን እያዛጉ ነዉ። ነፃነታችንን አይፈልጉም። የነሱ ብልፅግና በችጋራችን ላይ የተመሠረተ ነዉ። ስለዝህ ለዉጡን ቀልብሰዉ ወደነበርንበት ሊመልሱን እየተሯሯጡ ነዉ። ሩጫቸዉ በሁለት አቅጣጫ ነዉ። አንደኛዉ ሠላም ማደፍረስ ነዉ። በዝህ ረገድ ሰዉን ለመግደል እና ንብረት ለማዉደም ቅጥረኛን አሰልጥነዉ ከብዙ ገንዘብ ጋር አሰማርቷል። በተለያዩ ቦታዎች በየቀኑ ቦምብ እየተያዘ ነዉ። በየቦታዉ ሰዉ ሲሞት እና ንብረት ሲወድም ስጋት ይሰፍናል። የኢትዮጵያ ህዝብ ሠላም ካጣ የዶር አብይን አስተዳደር ጠልቶ የጅቦችን አገዛዝ ይመኛል። ያኔ ጅብ የሚፈልገዉን ያገኛል።
ሁለተኛዉ ደግሞ የኢኮኖሚ አሻጥር ነዉ። ጅቦች በተደራጀ ሌብነት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በበላይነት ተቆጣጥሯል። ብዙ ሸቀጦች በእነሱ እጅ ነዉ። ይህን አቅም በመጠቀም የገበያን ነፃ ዉድድር ለማወክ አቅዷል። ገባያ ሲዛባ አርተፍሻል እጥረት ይፈጠራል። ይህ ህዝብን ለረሀብ ይዳርጋል። ህዝብ ደግሞ ሲራብ በዶር አብይ አስተዳደር ላይ ይነሳል። በዝህ መሀል ጅብ ወደ ስልጣኑ ይመለሳል። ስሌቱ ይህን ይመስላል።
ስለዝህ ምን እናድርግ? ዋናዉ ጉዳይ ይህ ነዉ። ተጨማሪ ነፃነትን እንጅ ባርነትን አንሻም! ያገኘነዉን ዉጤት ለማስጠበቅ እና ተጨማሪ ስኬት ለማስመዝገብ ደግሞ ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋፅኦ ማድረግ አለብን።
1. እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በያለበት የሀገሩ ደህንነት ሆኖ የጅቦችን እንቅስቃሴ በአንክሮ መከታተል አለበት። አዲስ ነገር ባዬ ጊዜ በመረጃ አስደግፎ ለፀጥታ አካላት ያሳዉቅ። ሰላማችን በእጃችን ላይ ነዉ።
2. የኢኮኖሚ ችግርን በተመለከተ
ሀ. አያንዳንዳችን አሻጥረኞችን እንከታተል። ችግር ከተከሰተ ተጠያቂዉ መንግስት ሳይሆን የቀን ጅብ መሆኑ ከወዲሁ ይታወቅ።
ለ. ሀገር ወዳድ በለሀብቶች የሚፈጠሩ ክፍተቶችን ለመሙላት ከወዲሁ ዝግጅት ያድርጉ።
ሐ. መንግስት ችግሮችን ወደ ዕድል ይቀይር። የኢኮኖሚ አሻጥረኞችን በጥብቅ ተከታትሎ ንብረታቸዉን በመዉረስ ለህዝብ ጥቅም ያዉል። በቦታቸዉ ደግሞ ስራ አጥ ወጣቶችን አሰልጥኖ እና አደራጅቶ ያስገባ። ጫዉ ለራሱ ሲል ይጣፍጣል።
3. የኢትዮጵያ የፀጥታ ሀይል አባላት ከህዝብ ጋር እጅና ጓንት በመሆን ለሀገራቸዉ አንድነት እና ሠላም ዘብ መቆም አለባቸዉ።
ህብረታችን የማይንደዉ ተራራ የለም! የተባበረ ህዝብ ሁሌም አሸናፊ ነዉ!
ሠላም ዋሉ!

► መረጃ ፎረም - JOIN US

lørdag 26. mai 2018

የኢትዮጵያ ትግልና የአንዳርጋቸው ጽጌ ግንኙነት ለምን የቁርባን ግንኙነት ሆነ?! (መስቀሉ አየለ)


መስቀሉ አየለ
Andargachew Tsige is British national
Andargachew Tsige's father Tsige Habtemariam.
አቶ ጽጌ ሃብተማርያም
የአንዳርጋቸው አባት አቶ ጽጌ ስድስት እህትና ወንድሞቻቸውን አይናቸው እያየ ለጣሊያን ባደሩ ባንዳዎች እንደ አይሲስ በገጀራ ሲታረዱ እሳቸውና አንዲት እህታቸው ብቻ ነበሩ የተረፉት። እህቲቱ ባዩት ሁኔታ ልባቸው ከተሰበረበት አልጠገን ብሎ ከሰው ሳይነጋገሩ፣ በህጻንነታቸው መንኩሰው በዘጠና አመታቸው ሞቱ። አቶ ጽጌ ግን አርበኞቹን የሚመሩ አንድ የታወቁ ደጃዝማች አግኝተዋቸው ለአንድ ጉራጌ ገበሬ ደብዳቤ ጽፈውና ማህተም አትመው ጦርነቱ እስኪያልቅ ድረስ አደራ ሰጥተዋቸው ወደ ግንባር ሄደዋል።ያን ግዜ ብላቴናው ጽጌ እድሜያቸው ስድስት ወይንም ሰባት ቢሆን ነው፤እርግጡን አላውቀውም; እንደ እከሌ ልጅ ባክል ነው ይላሉ።
ጦርነቱ ሲያልቅ አርበኛው ደጃዝማች አልተመለሱም።ስለሆነም ባንዲራ ስትነሳና ንጉሱ ወደ አገር ውስጥ ሲመለሱ የጉራጌው ባላባት አራት አመት ሙሉ የያዙዋቸውን አቶ ጽጌን አዲስ አበባ ወስደው ንጉሱ ከቤተክርስቲያን ሲመለሱ እግራቸው ስር ተደፍተው አቤት አሉ፤ “ምን ሆነሃል?” ሲባሉ ደብዳቤውን እና “ብላቴናውን ጼጌ ሃብተማርያምን ተረከቡኝ፤ ስመ እግዚአብሔር ጠርቸ የተቀበልኩት አደራ ነው” አሉ። ታሪካቸው ቢነበብ ልብ የሚነካ ሆኖ ተገኘ። ደጃዝማቹም በህይወት አልተመለሱምና ንጉሱ ብላቴናውን በጉዲፈቻ ተቀብለው አዳሪ ትምህርት ቤት አስገቡዋቸው። የመጀመሪያውም የፊደል ሰራዊት አባል ሆነው ትምህርታቸውን አጠናቀቁ።
አቶ ጽጌ ሃብተማርያም በቀይ ሽብር ዘመን እንደገና የአንድ ልጃቸውን አስከሬን በመቶ ብር ገዝተዋል፤ ራሳቸውም ተሸክመው ከእስር ቤት እንዲያወጡ ተገደዋል። በዚህም የተነሳ በዚህች አገር ላይ ያለው ውስብስብ ፖለቲካ አንዳርጋቸውን በአባቱ በኩል ዘር አልባ አድርጎ አስቀርቶታትል። እርሱ ዘር ማንዘሮቹ ዋጋ በከፈሉበት አገር የባንዳዎቹ የልጅ ልጆች ደግሞ እርሱን አስረው በክፋታቸው ልክ እልሃቸውን ተወጥተውበታል። የአንዳርጋችውም ጽናቱ ፣ስለ አገርና ነጻነት ያለው ጥልቅ ፍልስፍና እንዲሁም አርባ አመት ሙሉ ያደረገው ያልተቋረጠ ተጋድሎ ይህን እየሰማና እያየ ማደጉ ነው። አረጋዊው ጽጌ ሃብተ ማርያምም ሶስት እሩቡን ወጥተው በአራተኛው እሩብ የእድሜ መገዳደጃ ላይ ማረሚያ ቤት ደጃፍ ቆመዋል ስንል ግብግቡ የተጀመረው ከሶስት ትውልድ በፊት ነው ለማለት ነው።መለስ ዜናዊ ይኼንን ስለሚያውቅ ቤተሰቡን በሙሉ “The Militant Family” ብሎ ይጠራው ነበር ።

torsdag 26. april 2018

Ethiopia: A Call for Worldwide Remittance Embargo

To all Ethiopians who are concerned about the dire fate of our country and eager in shortening the suffering of our people under the brutal Woyane regime.
Credible evidences coming from various sources indicate that the TPLF-led regime is immersed in a major political, economic, and security crises. It has come to light that, by all indicators and measures, the regime is in big economic collapse.
A recently leaked document authored by the so-called National Security Council confirms the regime’s anxiety about the economic crisis it has faced in recent months.  This document admits that:
  • Foreign aid has been reduced due to the regime’s worst human rights record;
  • Tourism has shrunk due to the instability throughout the country;
  • Wealthy people and foreign investors have started migrating their money out of the country; and
The regime is therefore convinced that these and other factors are contributing to the general economic crisis.
Meanwhile, in his report to TPLF parliament early November 2017, the Governor of the National Bank highlighted the serious shortage of foreign currency and warned that unless this shortage is resolved in a short period of time, it will aggravate the economic crisis.
Currently, the foreign currency shortage has reached to a level where even regime-run organizations including those which are used for surveillance and repressive purposes, such as Ethiotelecom, are defaulting on their foreign financial obligations. Further, these organizations reported that their inability to import equipment and hardware due to lack of foreign currencies has hampered their operations. As the foreign currency reserve of the country plummeted from $3 billion to $700 million, importers revealed to domestic media that they should wait for more than a year before they receive a Letter of Credit for their imports and even then, they only get a fraction of what they ask for.
As other sources of foreign currency dry up, the regime is placing its hope on the remittance of Diaspora Ethiopians to pick up the slack. The regime has publicly stated that the magnitude of the remittance from Ethiopians living and/or working abroad reaches over $4 billion per year.
There are a few fundamental facts that each Ethiopian needs to keep in mind when discussing the issue of foreign currency in relation to Ethiopia:
  1. The wealth and economy of the country including the foreign trade sectors are vastly controlled by TPLF-owned and affiliated entities such as Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFFORT); Tigray Development Association (TDA), and Relief Society of Tigray (REST);
  2. Those who benefit or hurt by the availability or shortage of foreign currency are mostly the above mentioned TPLF organizations and numerous companies owned by them;
  3. The economic/financial crunch the regime is facing currently will undermine the material, technological and economic capability of its security and police forces that are used to suppress, maim and kill Ethiopians;
  4. Crippling the regime’s economic backbone is a necessary form of struggle to shorten its political lifespan, and depriving the regime access to foreign currencies plays a critical role in this respect.
As every Ethiopian would note, at this moment our people are paying huge sacrifices to regain their freedom and ownership of their beloved country. The popular uprising of the past two years has dragged the regime into a huge crisis despite the fact that it is costing our people very dearly. The political and economic crises the regime is facing right now are in one way or another the fruits of the tenacious popular struggle. However, to ensure that this ever-growing popular struggle becomes victorious, it requires everyone’s action and involvement.  In this regard, we must recognize that Diaspora Ethiopians have a unique opportunity and capacity to undermine the regime’s economic and political power.
At this point, the money we Ethiopians in the Diaspora remit to our relatives back home is the only source of foreign currency for the regime.  Depriving the regime access to this hard currency is a power we have in our hands that we can and must use to exacerbate the regime’s economic crisis and constrain its ability to stifle and repress our people. It must be remembered that we have the responsibility and the ability to weaken the economic muscle of the regime, to shorten the suffering of our people, and ensure that their dear sacrifices are leading to victory.
The Worldwide Ethiopian Joint Task Force is therefore calling upon fellow Ethiopians in the Diaspora to stop remitting money through money transfer channels that allow the regime to acquire the hard currency.
Respectfully and on behalf of the people of Ethiopia, the Task Force calls up on everyone who wants to see an end to the suffering of our people to implement the following strategies and actions:
  1. Stop sending foreign currencies through the formal channels such as Western Union and Money Gram. The following alternative ways are suggested to send money that are deemed to minimize the chance of the regime accessing the hard currency:
    • Ethiopian-owned convenience stores and individuals in your community who are providing money transfer services; ensure they are not regime-affiliated.
    • Individuals in your community who have relatives in Ethiopia that are keen on exchanging Ethiopian birr for hard currency, often at a much better exchange rate than what the banks in Ethiopia offer. These folks often use the hard currency to import goods and services directly for their domestic businesses.
    • Send money through friends and acquaintances travelling to Ethiopia. This allows your relatives to exchange the hard currency in the black market at a higher rate than what the banks offer.
    • Send goods such as laptops and cell phones instead of money; your relatives will sell them for a much better value than they will gain by exchanging the dollar to birr in the bank.
  2. If the formal money transfer channels such as Western Union and Money Gram are your only option and you must send money to Ethiopia, depending on the financial needs of your relatives, the Task Force encourages you to consider reducing the amount and/or the frequency of your remittance by up to 30 percent.
  3. If your relatives in Ethiopia are financially well-off and your remittance has a relatively minimal impact on their economic well-being, the Task Force encourages you to consider stopping sending money altogether for at least a limited time as a show of support to the life-and-death struggle of our people.
  4. As the leaked National Security Council document admitted and the reality on the ground attests, the two-year long political and economic uncertainty is forcing wealthy Ethiopians (most of whom are regime-affiliated) to migrate and money-launder their wealth abroad. Considering this and the desperate need of the regime for hard currency, transferring money to Ethiopia now for commercial or investment ventures will do more harm than good to Ethiopia and Ethiopians. The Task Force therefore calls up on Diaspora Ethiopians who plan to invest in Ethiopia to cancel, delay, or limit their plans or activities for the time being. Doing so will not only support the popular struggle; it will also safeguard your hard-earned money given the uncertain economic and political climate in the country.
The people of Ethiopia will be victorious!
Long Live Ethiopia in glory!
Worldwide Ethiopian Joint Task Force

onsdag 25. april 2018

ከጉራ ፋርዳ የተፈናቀለዉ የአማራ ህዝብ ምን ዉስጥ ገባ? አሁን በምን አይነት መከራስ ዉስጥ ይገኛል?

ሰዉ ልጆች በርሃብ እንዲሞቱ በድፍረት የፈረደዉ ብአዴን:- የጉራፋርዳ አማራ ተፈናቃይ ነገር
————-
የባርነት ሀሳብ ተሸካሚዉ ብአዴን ነጻነት እና እኩልነት የሚባሉ ነገሮች መኖራቸዉን ያዉቅ ይሆን?:- እዉን ገዱስ የሰዉ ቁመት አለዉ?
——-
ሸንቁጥ አየለ
=======
የግል ገጠመኜ እንደ መነሻ:-
————
-ገዱ ሰሞኑን ጎንደር ላይ ለተገኘዉ አቢይ “ጠቅላይ ሚኒስቴር ካሁን ብኋላ ለህዝቦች ነጻነት ፍትሃዊነት: እና እኩልነት እንዲሰሩ አሳስባለዉ” ብሎ የተናገረዉን ንግግር እደመጥሁ ገዱ ድራማ እየሰራ ነዉ እዉን ገዱ እና ብ አዴኖች የነጻነት ቁመት አላቸዉ የሚል ጥያቄ በህሊናዬ ቢነሳ የነዚህን ሰዎች ሁኔታ የሚዳሥሱ ማህደሮችን ማሰስ ጀመርኩ::
– ከጥቂት አመታት በፊት ወደ አስር የሚጠጉ ትልልቅ እና አለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በጋራ የሚተገብሩት እና ከሚሊዮን በላይ ሰዎችን በመላ ሀገሪቱ የሚረዳ አንድ የሰበአዊ ርዳታ ፕሮግራም ቅድመ ማስተንቀቂያን ዘርፍ አስተባብር ነበር::በተለይም ይሄ ፕሮግራም የራሱ የዳታቤዝ እና ፈጣን የመረጃ ልዉዉጥ ከመላ ሀገሪቱ እንዲኖረዉ ማድረግ ችለንም ነበር::ዳታቤዙንም አስተባብር ስለነበረ ከመላ ሀገሪቱ ካሉ ወረዳዎች የርሃብ: እና የልዩ ልዩ የአደጋ መረጃዎች በሰዓታት ዉስጥ ይደርሱን ነበር:: እርዳታዉ የሚገኘዉ ደግሞ ከአሜሪካ መንግስት ስለነበረ የአሜሪካ መንግስት ምንም ያህል ሚሊዮን ቁጥር ያለዉ ተረጅ ምግብ ይፈልጋል ብለን መረጃ አቀናብረን ካቀረብን ያለምንም ማወላወል በቂ ምግብ ያቀርብ ነበር::ፈረንጅ አለቆቻችን በጣም የሚገርም ባህሪያቸዉ መረጃ ካቀረብንላቸዉ በፍጥነት ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ከሚገኘዉ የአሜሪካ እርዳታ ጽፈት ቤት ጋር መረጃ በመለዋወጥ በቂ ምግብ ዝግጁ እንዲሆን ይሰሩ ነበር::
-በዚህ አጋጣሚ ዉስጥ የትግራይ እና የኦሮሚያ የወረዳ እና የክልል አመራሮች ለተራቡ ሰዎች የተሻለ የእርዳታ ምላሽ ለመስጠት ሲተጉ አስተዉል ነበር::በተለይም የትግራይ የወረዳ አስተዳዳሪዎች ክልል ላይ ያሉ ሀላፊዎች የተዛባ ዉሳኔ ወስነዉ በወረዳ ያለዉ ርሃብተኛ እህል የማይደርሰዉ ከሆነ አጥብቀዉ ሲከራከሩ ወደ ኋላ አይሉም ነበር::የኦሮሚያ የወረዳ አስተዳዳሪዎች ከሞላ ጎደል ቢያንስ የርሃብተኛ ቁጥር ላለመደበቅ ሙከራ ያደርጉ ነበር::
-በተለይም በአመታዊ የምግብ ዋስትና ጥናት ወቅት (የተባበሩት መንግስታት የሚሳተፍበት እና የሚመራዉም) የኦሮሚያ የወረዳ ባለስልጣናት የሚያሳዩት ትጋት መልካም ነበር::ኦሮሚያ ላይ በክልል ደረጃ የጦፈ ክርክር ሲደረግ እና የምግብ ዋስትና ጥናቱ እንዲጸድቅ ሙሉ ድጋፍ ለማድረግ የክልልሉ መንግስት ሲታገል አማራ ክልል ግን ትርክቱ ሌላ ነበር:: ሰዎች በርሃብ ማለቃቸዉን እንደ ጀብዱ የሚቆጥሩት የብ አዴን አመራሮች የተራበ ካለ ከብቱን እና የቤት ንብረቱን ሸጦ ይብላ ካልተሳካለትም ይሰደድ ሲሉ ይመልሱ ነበር::
የባርነት ሀሳብ ተሸካሚዉ ብአዴንን ማሳያ ነጥቦች
—————–
አመታዊ የምግብ ዋስትና ጥናት ሲደረግ የብአዴን ባለስልጣናት ከወረዳ እስከ ክልል አንድ አይነት ቋንቋ እና ክፋት ያራምዳሉ::ይሄዉም ለምሳሌ የተቋማት የጋራ የምግብ ዋስትና ጥናት 2ሚሊዮን ህዝብ በአማራ ክልል ርሃብተኛ አለ ብሎ ሪፖርት ቢያደርግ “የለም ይሄ ጥገኝነትን ለማስፋፋት ነዉ::በክልላችን ከ200 ሽህ በላይ ርሃብተኛ የለም::ካለም ቻይናም የሚያልቀዉ አልቆ ነዉ ወደ እድገት ጎዳና የገባዉ” በማለት ይከራከሩና ጥናቱን ዉድቅ ያደርጉታል::
– አሁንም የተቋማት የጋራ የምግብ ዋስትና ጥናት 1 ሚሊዮን ህዝብ በአማራ ክልል ርሃብተኛ አለ ብሎ ካቀረበም ” የለም በክልላችን ያለዉ ርሃብተኛ መቶ ሽህ ብቻ ነዉ” ሲሉ ጥናቱን ዉድቅ ያደርጉታል:: አንዳንድ እልህኛ እና እዉነተኛ ባለሞያዎች አሉ::በተለይም የተወሰነ ነጻነት ያላቸዉ እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች ወይም መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የሚወከሉ ባለሞያዎች ወጥረዉ ይከራከራሉ::
-ከክልል ባለስልጣናት እስከ ዞን ባለስልጣናት ብሎም እስከ ወረዳ ባለስልጣናት አንድ የሚመልሱት መልስ “ከራበዉ ከብቱን ሸጦ ይብላ::ጥሪት ሀብቱን ሸጦ ይብላ::ካልቻለም ይሰደድ::ካስፈለገም ይሙት::ይሄ እናንተ የምታጠኑት ጥናት ግን ጥገኝነት እና ስንፍና የሚያስፋፋ የተረጅነት መንፈስ የሚያበረታታ ስለሆነ አንቀበለዉም” ብለዉ ቁጭ ይላሉ:: በመላዉ ሀገር ህዝብ ችግር ላይ ሲወድቅ መንግስት ህዝብን በመደጎም ህይወቱን እንደሚያተርፍ ግን ጠፍቷቸዉ አይደለም::ሌላዉ ቀርቶ አሜሪካ ዉስጥ ዜጎች ሲቸገሩ በመንግስታቸዉ ተደጉመዉ የገጠማቸዉን ክፉ ቀን እንደሚያልፉት ብአዴኖች ያዉቃሉ::ሆኖም የባርነት መንፈስ ዉስጥ ናቸዉ እና የሚያልቀዉ አልቆ..ሲሉ ሳይዘገንናቸዉ መልስ ይሰጣሉ::
– ይሄን አይነት መልስ በተለይም በጎንደር እና በወሎ ልዩ ልዩ ወረዳዎች ሰዎች በርሃብ እዬሞቱ የወረዳ ባለስልጣናት ደጋግመዉ ቢመልሱልን አንድ ጊዜ አሜሪካኖቹን ቢፈሩ ብለን የአሜሪካ እርዳታ ድርጅት ባለስልጣናትን ወደ ወረዳዎቹ እንዲሄዱ አግባብተን በዬወረዳዎች ጉብኝት እንዲያደርጉ ሆኖ ነበር::ባለስልጣናቱም ባዩት ነገር አዝነዉ የክልል እና የፌደራል ባለስልጣናትን ለማነጋጋረ ሞከሩ::የፌደራል ባለስልጣናት እኛ በክልል ዉሳኔ ዉስጥ አንገባም ብለዉ ቁጭ::በየወረዳዎቹ ግን ሰዎች እየሞቱ ነበር::
– ይሄ ሁሉ ሁኔታ እየተከናወነ ሳለ የቅድመ ማስጠንቀቂያ የዳታቤዝ ስልጠና በሚል አንድ ስልጠና አዘጋጅተን ነበር::የመረጃ: የዉሳኔ እና በርሃብ ላይ ያለን ህዝብ ህይወት የመታደግ ቁርኝት የሚያሳይ አንድ ድራማ በስልጠናዉ መካከል እዲካተት አድርጌ ነበር::ድራማዉን በደንብ አስቤበት ስላዘጋጀሁት ተዋንያን ሆነዉም የሚተዉኑት ሰዎችን ከስልጠናዉ ተሳታፊዎች መሃከል በጥንቃቄ መርጫቸዉ ነበር::በዚህ መሰረትም ዉሳኔ ሰጭ ሆኖ እንዲቀመጥ ግን ምንም ዉሳኔ መስጠት የማይችል ሆኖ እንዲተዉን ያደረግሁት የድራማዉ ተዋናይ ደግሞ አንድ የብአዴን ባለስልጣን የነበረ ሰዉ ነበር::ስም እዚህ አላነሳም::ግን ባለስልጣኑ የዋዛ ሹመት አይደለም የነበረዉ::
– እናም በትወናዉ ዉስጥ በጣም በሚገርም ሁኔታ የበላዮቹን እያሰበ እና በፍርሃት ተሸብቦ ህዝብ እየሞተ የተለያዬ ምክንያት እየሰጠ ምንም ነገር ሳይወስን ቁጭ ብሎ ሲንገታገት ይስተዋላል::በመጨረሻም የሚሞተዉ ሰዉ ሳይሆን የሚያሳስበዉ የእርሱ ስልጣን ሆኑ ከስልጣኑ እንዳይነሳ ሲጨነቅ እና ሲርበተበት ይታያል::ድራማዉን በሚገርም ሁኔታ ተዉኖት ነበር::በስልጠና ሂደት ዉስጥ “role play” ብለን የምንጠራዉ የዚህ አይነት ድራማ በስልጠና ህደት ዉስጥ ሁኔታዎችን ከብዙ ቃላት በላይ ቁልጭ አድርጎ እንደሚያሳይ የሚያዉቅ ያዉቀዋል::
-ድራማዉን ተዉነዉ ሲጨርሱ ለብቻችን ስንሆን ይሄን የብአዴን ባለስልጣን አንድ ጥያቄ ጠየቅሁት::”ድራማዉን እየሰራህ ምን ተሰማህ?” የሚል ጥያቄ:: :አቀርቅሮ ዝም አለ::አሁንም ደግሜ ጠዬቅሁት::አልመለሰልኝም::ለሶስተኛ ጊዜ ስጠይቀዉ በጣም አዝኖ ” ባርነት ነዉ የተሰማኝ” ብሎኝ ቁጭ:: ድንገት ሳላስበዉ ሰፊ ፈገታ እፊቴ ላይ ታዬ::እኔ ፈገግ ስል::እሱም ቀና ብሎ ሲያዬኝ ፊት ለፊት ተያዬን:: ለምን ፈገግ እንዳልኩ ልቤን ያነበበዉ ይመስል “ይገባኛል::ምን እንደሚያስቅህ ይገባኛል::” አለኝ::ይሄ የብአዴን ባለስልጣን የኔን አቋም በብዙ መንገድ ጠንቅቆ ያዉቃል ብቻ ሳይሆን ገና አንድ አረፍተ ነገር ስናገር ምን እያሰብኩ እንደሆነ የሚረዳ ይመስለኛል::
– እኔም ምንም እንኳን ዉስጤን እንዳነበበዉ ባዉቅም “አይገባህም::አይገባህም::አይገባህም::” ስለ ሶስት ጊዜ መለስኩለት::እርሱም በማዘን እና በጥልቅ ብስጭት ” የሆነ ትምክህት አለብህ::ስለሀገር እና ህዝብ አንተ ብቻ የምትቆረቆር ይመስልሃል::እኛ እዚህ ኢህኣዴግ ዉስጥ ያለን ሰዎች ህዝብ ቢያልቅ በርሃብ ከምድረ ገጽ ቢጠፋ የምንፈልግ ይመስልሃል::?” ሲል ተቆጣኝ::
– አሁንም ፈገግ ብዬ እያዬሁት ነበር::ፈገታዬ ደግሞ አዎና የሚል ነበር::እርሱም አንብቦታል መሰለኝ “ቆይ ግን ምን እንድናደርግ ነዉ የምትፈልገዉ::ከድርጅቱ አቅጣጣ ዉጭ ምን እናድርግ?” ሲል ጠዬቀኝ::አሁን ግን የመሸነፍ ስሜት የተሰማዉ ይመስላል::እኔም አጋጣሚዉ ተመቸኝ እና መልሴን ሰጠሁት::”ኢህአዴግ ምንም አቅጣጫ አልሰጣችሁም::ህዉሃቶች እና ኦህዴዶች ስለተራበ ህዝባቸዉ ወገባቸዉን ይዘዉ ሲከራከሩ እናንተ ግን የተራበ ህዝባችሁን ከፈለገዉ ከብቱን ሽጦ ይብላ አለዚያም ይሰደድ የምትሉ አይደላችሁም? እና እራሳችሁ ብአዴኖች የፈጠራችሁት ችግር ነዉ::ፌደራል ላይ ያሉትም ባለስልጣን ለአማራአ ክልል ብቻ የተለዬ ዉሳኔ አይሰጡም::ወይም ይሰጣሉ ብዬ አላስብም::” ስል አብራራሁለት::
– “እና…” ይሄ ባለስልጣን ተኮሳተር::ሲኮሳተር ፈገግ ብዬ “እናማ የድራማዉ ተዋናይ የተወነዉ ሚና ብአዴኖች ጋ ያለ መሰለኝ?” ስል አብራራሁለት:: በዚህ ቅጽበት እንደ እሳት ቱግ አለ::” ገባኝ::ለካ ይሄን የስልጠና ፕሮግራም ስታዘጋጅ ይሄን ድራማ የጻፍከዉ እኛን ለመስደብ ነዋ::” እየተመናጨቀ ጥሎኝ ሄደ::
– ጥቂት እንደሄደ ስሙን ጠራሁት::ዞር አለ:: “እንደዉነቱ ከሆነ የድራማዉ ዋናዉ ግብ የብአዴንን ባህሪ ማሳዬት ነዉ::ለምሳሌ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳታ ቤዝ ትግራይ እና ኦሮሚያ በእኛ አስተባባሪነት እንድሰራላቸዉ ፈቃደኛ ሲሆኑ የአማራ ክልል ግን የፌደራልን ፈቃድ ጠይቄ ነዉ ዳታቤዙን እንድትሰሩልን የምፈቅደዉ እያላችሁ ነዉ::ትግራይ ክልል እና ኦሮምያ ፌደራል እንጠይቃለን አላሉም::አማራ ክልል ይሄን አቋም ከዬት አመጣዉ?” ስል ጠዬቅሁት:: እርሱም ወደኔ እያስተዋለ “እና ?” ሲል ጠዬቀኝ::እኔም “ድራማዉ ዉስጥ ያለዉ ሚና ጉዳይ ነዋ” ስል መለስኩለት:: እናም እየተቆጣ ጥሎኝ ሄደ::
-የሚገርመዉ ከአንድ ወረዳ ወደ ክልል የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃ ለመድረስ ከአንድ ወር እስከ ሶስት ወራትን ይፈጃል::መረጃዉም በመንገድ ላይ ሊጠፋ ይችላል::በዳታቤዙ ቅድመ ማስጠንቀቂያዉ ስርዓት ቢዘረጋለት ግን በሰዓታት ዉስጥ በያንዳንዱ የክልሉ ወረዳዎች የሚደርስ አደጋ ሁሉ ለባለስልጣናቱ ይደርሳል::ፈጣን ዉሳኔም ማሳለፍ ይችላሉ::እንዲህ አይነቱን አሰራር ለመዘርጋት ነዉ እንግዲህ የአማራ ክልል የብአዴን ባለስልጣናት የፌደራል መንግስትን ተይቀን የሚሉት::ለነገሩ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳታቤዝ እንዲሰራላቸዉ የፈቀዱትም የኦሮሚያ እና የትግራይ ክልልሎች አሰራሩ ሳይዘረጋላቸዉ በሀሳብ የቀረበት ብዙ ምክንያት ተከተለ::
የገዱ ቁመት ምን ያህል ነዉ:- ገዱ ከማን ነዉ ነጻነትን እና ፍትሃዊ አስተዳደርን የሚጠብቀዉ
————————-
ገዱ ሰሞኑን አቢይን ጎንደር ጋብዞት ሳለ የጀግና እና የነጻ ሰዉ የሚመስል ሀሳብ አንስቶ ባይ ነዉ ይሄ ሁሉ ትዝታ የመጣብኝ::ጠቅላይ ሚንስቴር አቢይን “… ለነጻነት እና ለፍትህ እንዲሰሩ አሳስባለሁ…” ብሎ ቁጭ:: እኔ ደግሞ እዉን ገዱ ነጻነት የሚያዉቅ ሰዉ ነዉ ስል እራሴን ጠዬቄ ይሄን ጽሁፍ ማዘጋጀት ጀመርኩ::
የሰዉ ልጆች በርሃብ እንዲሞቱ የፈረደዉ ብአዴን:- የጉራፋርዳ አማራ ተፈናቃይ ነገር
————————
– ከላይ ባልኩት ፕሮጀክት ዉስጥ ስሰራ ግማሽ ሚሊዮን አማሮች ከጉራፋርዳ ሲባረሩ ለፈረንጅ አለቆቼ አንድ ጥናት አቅርቤላቸዉ ነበር::” እነዚህ የተፈናቀሉ አማሮች የሚበሉት የለም::የእኛ ፕሮጀክት ሊርዳቸዉ ከቻለ እኔ ደግሞ የአማራ ክልል ባለስልጣናትን ሄጄ አነጋግራለሁ::” ስል ሀሳብ አቀረብኩላቸዉ:: ፈረንጆቹ አለቆቼ በፍጥነት “በቂ ምግብ ስላለን ሰዎቹን እንረዳለን” የሚል መልስ ሰጡኝ እና እኔም ጉዜዬን ወደ ባህርዳር አደረግሁ::
-ባህርዳርም እንደደረስሁ የአማራ ክልል ባለስልጣናትን ማነጋገር ጀመርኩ:: ካነሳሁባቸዉም ነጥብ ዉስጥ “የአማራ ክልል ከጉራፋርዳ ለተፈናቀሉት አማሮች በደብረብርሃን ወይም በባህርዳር አለዚያም በሆነ ቦታ መጠለያ ካዘጋጀ የኛ ፕሮጀችት በቂ የምግብ እርዳታ ያቀርባል” የሚል ሀሳብ አቀርበሁላቸዉ:: እነዚህ ባለስልጣኖችም ከላይ እስከታች የመለሱልኝ መልስ አስደንጋጭ ነበር::ይሄዉም ” እነዚህ ከጉራፋርዳ የተፈናቀሉ አማራዎች የሰዉ ሀገር ሄደዉ የወረሩ ናቸዉ::ስለዚህ የአማራ ክልል በእነዚህ ሰዎች ጉዳይ አያገባንም” ሲሉ መልስ ሰጡ::ይሄ አቋም የተወሰኑ ባለስልጣኖች መስሎኝ ብዙዎቹን በሰዉም በግልም አነጋገርኳቸዉ:: መልሳቸው ግን ያዉ ነበር::ይባስ ብለዉም በግል የነገሩኝን ነገር በአደባባይ በሚዲያ ወጥተዉ ተናገሩ:: የሰዉ ሀገር ሄደዉ የወረሩ : ዛፍ የጨፈጨፉ ናቸዉ የሚል እና የጸረ አማራዉን የሽፈራዉ ሽጉጤን ንግግር የሚያጸድቅ ዉሳኔን የአማራ ክልል ይዞ ብቅ አለ::እዉን ይሄ ተረት ተረት እንጅ እዉነት ይመስላል?
-እናም በዚህ የአማራ ክልል የሚባል ዉስጥ የመሸጉ የጸረ አማራ ሀይላት አቋም የተነሳ ከአባቶቹ ሀገር ከጉራ ፋርዳ የተባረረዉ እና በሜዳ የተበተነዉ ግማሽ ሚሊዮን አማራ አለ አንዳች እርዳት በርሃብ እና በድህነት ብሎም በበሽታ እየተቀጠቀጠ እና እየሞተ አሁን ድረስ የትም ተበትኖ ይገኛል::ህጻናቱ በጎዳና ምናልባትም በበሽታ አልቀዋል:: አዛዉንት በብርድ እና በበሽታ አሸልበዋል::ጎልማሶች ከትዳራቸዉ ተናጥለዉ ትዳራቸዉ ፈርሶ የትም ለማኝ ሆነዋል::ግን ይሄ ህዝብ ምን ወገን አለዉ? ይሄንንስ ማን ይናገርለታል?
– እንግዲህ ይሄን ሳስብ ነዉ ገዱ የሚባለዉ የወያኔ ባሪያ ለሌላዉ የወያኔ ባሪያ ጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ የህዝብ ነጻነትን የተመለከተ ንግግር እያደረገ በህሊናዬ “የባርነት ሀሳብ ተሸካሚዉ ብአዴን ነጻነት እና እኩልነት የሚባሉ ነገሮች መኖራቸዉን ያዉቅ ይሆን?” የሚል ጥያቄ የተመላለሰብኝ::አማራ ነኝ ብለዉ ከአማራ አብራክ የወጡ እነ ገዱ አማራዉ በርሃብ : በዉርደት እና በስደት ሲጠፋ በምግብ እንኳን እራሱን እንዲመግብ እንርዳዉ የሚሉ የፈረንጅ ሰዎች ፈቃደኛ ሲሆኑ አባቶቹ በመሰረቱት ሀገሩ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚኖረዉን አማራ “የሰዉ ሀገር ሄዶ ስለወረረ ተፈናቅሎ በርሃብ ቢያልቅ አያገባንም” ሲሉ የተዘባበቱት የባርነት ሀሳብ ተሸካሚዎች እንጅ ምን ሊባሉ ይቻላሉ? እንጃ ደጋግሜ ሳስበዉ ለእነዚህ ሰዎች መግለጫ ቃል ያጥረኛል::
– በግል ህይወቴ ይቅር ባይ እንደሆንኩ አብሮኝ የኖረ ያዉቃል::በአማራ ህዝብ ላይ ወያኔ እና የወያኔ አገልጋይ እነ ብአዴን የሰሩትን ነገር ሳስብ ግን ነብዩ ሳሙኤል ህዝበ እስራኤል በጉዞ ላይ እያለ ባጠቁት ጠላቶች ላይ የፈጸመዉ ድርጊት ነዉ በህሊናዬ የሚመላለሰዉ:: መጽሀፈ ሳሙኤል ቀዳማይ 15 (32-33) :-
“ሳሙኤልም፦ የአማሌቅን ንጉሥ አጋግን አምጡልኝ አለ። አጋግም እየተንቀጠቀጠ ወደ እርሱ መጣ። አጋግም፦ በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን? አለ። ሳሙኤልም፦ ሰይፍህ ሴቶችን ልጆች አልባ እንዳደረገቻቸው እንዲሁ እናትህ በሴቶች መካከል ልጅ አልባ ትሆናለች አለ፤ ሳሙኤልም አጋግን በእግዚአብሔር ፊት በጌልገላ ቈራረጠው።”
እግዚአብሄር ይሄን የዋህ ህዝብ እንዲህ በጠላጠላትነት የተበቀሉትን ጠላቶች የሚመታበት ዘመን እንዳለ እሙን ነዉ::የዚህን የዋህ ህዝብ ጠላቶች አንድም በነብይ ወይም በጦረኛ ከምድረገጽ እግዚአብሄር እንደሚመታ አምናለሁ::ቀኑ ይመጣል::ይሄን ግን ነገርን በጊዜዉ ዉብ አድርጎ ለሚያከናዉን አምላክ ልተወዉ እና ወደ ተነሳሁበት ዋና ጥያቄ ልግባ::
-ይሄ ጥያቄ በየቀኑ በህሊናዬ እየተመላለሰ የሚበጠብጠብጠኝ ቢሆንም አሁን የገዱን የህዝብ ነጻነት ይከበር ንግግር እየሰማሁ ግን በህሊናዬ ጮክ ብሎ ተሰማኝ::እናም የባርነት አስተሳሰብ ተሸካሚዎቹ ብ አዴኖች ባይመልሱልኝም ህዝብ እንዲያስታዉሰዉ ከቻለም አንዳንድ እርዳታ ማድረግ ቢችል ጥያቄዉን ወደ አደባባይ አወጣሁት::
ጥያቄዉ:- ከጉራ ፋርዳ የተፈናቀለዉ የአማራ ህዝብ ምን ዉስጥ ገባ? አሁን በምን አይነት መከራስ ዉስጥ ይገኛል?
—————————————-
ከጉራ ፋርዳ የተፈናቀለዉ ግማሽ ሚሊዮን የአማራ ህዝብ (ወንዱ ሴቱ: ህጻናቱ: አዛዉንቱ) የት ነዉ አሁን ያለዉ? በጎዳና? በሞት መቃብር? በድህነት ዉስጥ? አሁንም እየተንከራተተ::
ለምሆኑ አሁን እነዚህን ዜጎች ወይም ወደፊት መልሶ ሊያቋቁማቸዉ: ሊያሰፍራቸዉ የሚችል አካል ማን ነዉ? ሌላዉ ቀርቶ መብታቸዉ ምን እንደሆነ አሳዉቆ መብታቸዉን እንዲጠይቁ ሊያደራጃቸዉ የሚችል አካልስ ማን ነዉ? የባርነት ሀሳብ ተሸካሚዉ ብአዴን ነጻነት እና እኩልነት የሚባሉ ነገሮች መኖራቸዉን ያዉቅ ይሆን?:- እዉን ገዱስ የሰዉ ቁመት አለዉ? ገዱ የሚመራዉ የባርነት ሀሳብ ተሸካሚ እንዲህ አይነት የህዝብ ጥያቄ ያነሳል ተብሎ መቼም አይጠበቅም::
-በአማራ ህዝብ የተደራጁ ድርጅቶች (የፖለቲካም ቢሆኑ : የሲቪልም ቢሆኑ) የዚህ ህዝብን መልሶ መቋቋም ሊያነሱለት ይገባል ብዬ አስባለሁ::በቅርቡ ከሶማሌ ክልል ለተፈናቀለዉ በሚሊዮን የሚጠጋ የኦሮሞ ህዝብ በዶክተር መራራ የሚመራዉ መድረክ እና ኦህዴድ ደጋግመዉ የተፈናቃይ ወገኖቻችንን የመልሶ መቋቋም ጥያቄዉን ወደ ህዝብ እያቀረቡለት ነው::ይሄም ይበል የሚያስብል ነዉ::
-ሆኖም ከጉራ ፋርዳ የተፈናቀሉ አማራዎች ሁኔታን ተቃዋሚዎችም: ሚዲያዎች ዝምታን የመረጡት እነዚህ ዜጎች ምን ስለበደሉ ነዉ? ጥያቄዬ ማለቂያ ለዉም::ስለሆነም እዚህ ጋ ማቆም አለብኝ::የገዱን “ህዝቡ ካሁን ብኋላ የፍትህ የነጻነት እና የዲሞክራሲ መፍትሄዎችን እንዲያገኝ ጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይን አሳስባለሁ” ብሎ የተናገረዉን ንግግር ሰምቼ እንደገና ነገሩ እንደ አዲስ ኩልል ብሎ በህሊናዬ ተመላለሰ::ገዱ የተባለ እና ብአዴን የተባለ የባርነት ተሸካሚዎች ለመሆኑ እነዚህ ከጉራፋርዳ የተፈናቀሉ እና ከሌላ አካባቢ የተፈናቀሉ አማራዎች ምግብ እንኳን እንዲያገኙ ወደፊት ይፈቅዱላቸዉ ይሆን?ምግብ ለሰዉ ልጅ የማይፈቅድ ሰዉ ስለ ነጻነት ያወራል ቢባል ታላቅ ቀልድ ነዉ::ምግብ ማግኘት ከመሰረታዊ የሰዉ ልጆች የሰበአዊ መብት ዉስጥ ይመደባልና::
– ብአዴን ዉስጥ የተሰገሰጉ የባርነት ሀሳብ ተሸካሚ የህዉሃት ባንዳዎች ግን እዉነት ነጻነት ምን እንደሆነ ከቶስ ያዉቃል? ሰዉ የራሱ ወገን ምግብ እንኳን ተመግቦ እንዳያድር የሚጨክን ህሊና ካለዉ በዉኑ እነ ገዱ : እነ አያሌዉ ጎበዜ: እነ አዲሱ ለገሰ: እነ እንቶኔ እነ እንቶኔ የሚባሉ ብአዴን ዉስጥ ከሃያ አመታት በላይ የመሸጉ ሰዎች በእዉኑ ነጻነትን ያዉቁታል ተብሎ ይጠበቃል? ሀሰት ነዉ::ዉሸት ነዉ::ፈጽሞ ነጻነት አያዉቁም::እነዚህ የባርነት ሀሳብ ተሸካሚዎች እንጅ:: አሁንስ ከነዚህ ሰዎች ህሊና የነጻነት ሀሰብ ይፈልቃል?ሀሰት::ለመሆኑስ ገዱ ለሚመራዉ ህዝብ የአማራ ህዝብ ነጻነት ለማጎናጽፍ ካሰብ ከማን ነዉ ነጻነትን እና ፍትሃዊ አስተዳደርን የሚጠብቀዉ? ለመሆኑስ የገዱ ቁመት ምን ያህል ነዉ?ቢያንስ ለሚመራዉ ህዝብ ምግብ የማግኘት መሰረታዊ የሰበአዊ መብቱን የሚያከብር ሰዉ ነዉ?

Shukshukta (ሹክሹክታ) - Solomon Tekalign ሰለሞን ተካልኝ ኡ ኡ ኡ እያለ ነው


fredag 13. april 2018

STER or LOGIN ትግራይ የኢትዮጵያ ሞተር ነች! ዶ/ር አብይም ትክክል ነው! ቅኔውን ይዘርፈዋል!

ትክክል ነው! ትግራይ የኢትዮጵያ ሞተር ነች! ሞተርም አይጠፋትም! ዶ/ር አብይም ቅኔውን ይዘርፈዋል!
ለምሳሌ! Getachew Shiferaw
ከስር ዝርዝሩ ላይ ያሉት ፋብሪካዎች ያላቸውን ሞተር እንኳ ብናሰላ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት መካከል ከ80 በመቶ በላይ ነው። የቀሩት፣ በሌላ ቦታ ያሉትን፣ የመከላከያ ሰራዊቱ ጀኔራሎች የሚቆጣጠሩት የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ሞተሮች ሲጨመሩ የዶ/ር አብይን አባባል እውነት ያደርገዋል!
No automatic alt text available.

søndag 8. april 2018

የኢትዮጵያም ትንሳዔ ይሁንልን ! (በአንዱ-ዓለም አራጌ)

ኢትዮጵያውያን በአገዛዝ ቀንበር ሥር ነበርን፤ አሁንም በነበርንበት ቀጥለናል። በኢትዮጵያ የኅላዌ ዘመን ሁሉ አገዛዝ ተለይቶን አያውቅም። ለአለፉት 27 ዓመታት የተጫነብን የአገዛዝ ቀንበር ደግሞ ከመቼውም ጊዜ የተለየ ነው። የተለየ ብቻ ሳይሆን የከፋም ነው። የከፋ ያልኩት ዘርን መሠረት ያደረገ በመሆኑ ነው። ዘርን መሠረት ያደረገው አገዛዝ በደምና ስጋ የተገመደውን የሕዝባችንን ቁርኝት ሳይቀር ለመበጠስ ትልቅ ተግዳሮት ጋርጦብን ነበር። ትዳሮች እንዲፈርሱ፣ ጉድኝቶች እንዲቀዘቅዙ፣ አለመተማመን በመሐከላችን እንዲነግሥ፣ በዘር ተቧድነን እንድንቆራቆዝ፣ ደም እንድንፋሰስ፣ አንዳችን ስለሌላው ልንሞት ሲገባን ሌላውን ለመግደል ያደባንበት ሁኔታ ተከስቷል። ይህን የመሰለው ሁኔታ የአገራችንን መሠረት እስከማናጋት የሚደርስ ተግዳሮት ሆኖ ነበር።
ከሁሉም በላይ ለሰው ዘር ሁሉ ቤዛ ስለሆነው መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በሚሰበክባቸው አብያተ ክርስትያናት ድረስ ዘልቆ በመግባት በዘር የመለያየት ሁኔታ መፈጠሩን በሐዘን እናስታውሳለን። በተለይ በውጭ አገራት በሚገኙ አብያተ ክርስትያናት ችግሩ ሥር የሰደደ መሆኑን እንገነዘባለን። የተለያዩ ብሔር ተወላጆች የራሳቸውን አብያተ ክርስትያናት ለመፍጠር የሔዱበት መንገድ ቅስምን የሚሰብር ነው። ብንችል ፈጣሪያችንንም ለመክፈል የምንተጋ ይመስላል። ይህ ሁኔታ ምን ያህል ከሰብአዊነት ጎዳና እያፈነገጥን እንደሆነ ብሎም ምን ዓይነት የሞራል ድቀት ውስጥ እንደምንገኝ ያሳያል።
አሁን የልዩነቱ ማዕበል ፀጥ ሲል ይሰማኛል። የልዩነቱ አቧራ ሲሰክን ይታየኛል። ከፊታችን ወደእኛ በሚገሰግሱ ዓመታት ከቆምንበት የመለያየት አዘቅት ወደ ሰማይ ጠቀስ የወንድማማችነት ተራራ ስንወጣ ይታየኛል።
ለዘመናት በአገራችን ላይ በደቀደቀው የአገዛዝ ጨለማ ላይ የብርሃን ፍንጣሬ ሲረጭ አያለሁ። ይህ የብርሃን ፍንጣሪ ለሁላችንም ወደሚያበራ የዴሞክራሲ ደማቅ ጀምበር እንዲለወጥ ከምኞት ባለፈ ሁላችንም ተቀዳሚ አጀንዳችን አድርገን እጅ ለእጅ ተያይዘን ልንታገል ይገባል። የዴሞክራሲና የፍትሕ ፀሐይ የወጣበት ምድር ሕዝቡን ፆም አያሳድርም። ምርቱን በልግሥና ይሰጣል። ቁራሽ ፍለጋ በአየር፣ በምድረ-በዳና በባሕር ከአገራችን የምንኮበልልበት ዘመን ላይመለስ ሲነጉድ ይታየኛል። ይህ እውነት ደምና ስጋ እንዲለብስ ሁላችንም የተተበተብንባቸውን የመለያየት ድሮች በጣጥሰን ለእውነተኛ ፍትሕና ዴሞክራሲ የፀና ሠላማዊ ትግል አበክረን ልናደርግ ይገባናል።
የክርስቶስ ትንሳዔ ዘመንን ከፍሏል። ሞትን በፍቅር ድል ነስቷል። ጥላቻን በፍቅር ገድሏል። ይህ የትንሳዔ በዓል በየግል ሕይወታችን ለኢትዮጵያውያን ሁሉ የስኬትና የትንሳዔ ብሥራት እንዲሆንልን ከልብ እመኛለሁ። እንደአገር ከአገዛዝ፣ ከችጋርና ከጥላቻ ጨለማ ወደ የዴሞክራሲ፣ የብልፅግናና የፍቅር ደማቅ ንጋት የምንሸጋገርበት ይሁንልን።
“በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ” እንደሚል የቆሰለው ልባችን ሊፈወስ ዘመን ደጃችን ላይ ቆሟል። አሁኑኑ የልባችንን በርና መስኮት ለፍቅር እንክፈት። ከፍ ብለው በሚታዩት የቤተ እምነቶቻችን ጉልላት ላይ የእውነት፣ የፍትሕ፣ የሠላም፣ የፍቅርና የወንድማማችነት አርማዎቻችን ከፍ ብለው ይውለብለቡ። የሃይማኖት መሪዎቻችን የሚሞተውን የሰው ልጅ ሳይሆን ዘላለማዊውን ጌታ በመፍራት እንደዓላማ ሰንደቅ ከሩቅ የሚታዩ የእውነትና የፍቅር ተምሣሌቶች እንዲሆኑ እመኛለሁ።
ትንሳዔ ስለፍቅር ፍቅርም ስለትንሳዔ ነው።
የኢትዮጵያን ትንሳዔ በፍቅር፣ በፍትሕና በዴሞክራሲ ላይ እናንፅ!
ጥላቻን በማስወገድ ፍቅርን እንደቡልኮ እንልበስ – እንፈወስ።

lørdag 31. mars 2018

Ethiopia govt must free Eskinder Nega, other political prisoners – U.S. Senator Rubio

U.S. Senator Rubio
The United States Senator for Florida, Marco Rubio
(Africa News) — The United States Senator for Florida, Marco Rubio, has waded into the recent re-arrest of Ethiopian journalists and other political prisoners, urging the Ethiopian government to release them.
Tweeting the AP report on the re-arrest, Rubio’s PressShop wrote on Friday: “Ethiopian journalist Eskinder Nega, who was recently released after 7 years in prison on false charges, was just re-arrested.
“I urge the Ethiopian government to release him and other political prisoners. #expressionNOToppresion.” The Senator joins a long list of other rights groups – local and international, piling pressure on the regime to release the detainees.

They were arrested for attending an unauthorized gathering and use of a banned national flag. The gathering in question was a welcome party for recently released prisoners in the capital of Amhara regional state, Bahir Dar.
Aside Nega, others picked up during the gathering were, Andualem Aragie, leader of Ethiopian opposition UDJ party, journalist Temesgen Desalegn and bloggers Befeqadu Hailu and Zelalem Workagegnehu.
The multiple-award winning Nega who was jailed in 2011 on terrorism charges is on record to have said he was ready to return to jail if the democracy was not respected.
“I am prepared to go back to prison. What I am not prepared to do is give up. We will continue to press and struggle for freedom of expression and democracy,” the 47-year-old said in an interview days after he was freed.
According to regulations of the Command Post overseeing the latest state of emergency declared in mid-February, people are prohibited from gatherings that do not have the approval of relevant authorities.
On the subject of the flag, the gathering used the Ethiopian plain flag, which does not have the blue disc contrary to law.
A proclamation regarding the use of the Ethiopian flag prohibits the display of the flag without the emblem at its center and those contravening the law could be sentenced to up to a year and a half in prison.
Some Ethiopian opposition groups have on several occasions expressed their displeasure with the new flag arguing that the ruling coalition, EPRDF blue disc star symbolises ethnic division.
The country is to swear in a new Prime Minister Abiy Ahmed from the protest-hit Oromia region. He takes the mantle after the resignation of Hailemariam Desalegn who quit to allow promised reforms to be pursued.

mandag 26. mars 2018

Ethiopia re-arrests recently freed politicians, journalists


Ethiopian security forces have re-arrested a number of recently freed politicians.
On March 25, 2018, some of recently freed politicians and journalists gathered at journalist Temesgen Desalegn’s house (Photo: Families of arrested journalists)
ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Ethiopian security forces have re-arrested a number of recently freed politicians and journalists as they gathered for a social event outside the capital, Addis Ababa, with family and friends, a lawyer said Monday.
Amha Mekonnen has represented a number of the detainees. The lawyer told the Associated Press the arrests Sunday afternoon occurred because they were accused of displaying a prohibited national flag. “I also understand they were accused of gathering en masse in violation of the state of emergency rule.”
Under Ethiopia’s latest state of emergency declared earlier this year, people are prohibited from such gatherings without authorities’ prior knowledge. A proclamation regarding the use of the Ethiopian flag prohibits the display of the flag without the emblem at its center and those contravening the law could be sentenced to up to a year and a half in prison.
Among those arrested are journalists Eskinder Nega and Temesgen Desalegn, politician Andualem Aragie and prominent blogger Befekadu Hailu.
Government officials were not immediately available for comment.
In a surprise move early this year, Ethiopia’s Prime Minister Hailemariam Desalegn announced that members of political parties and other individuals would be released from prison in an effort to open up the political space for all after months of the worst anti-government protests in a quarter-century.
Several dozen journalists, politicians, activists and others arrested under a previous state of emergency were freed. Since then, however, the prime minister announced his plans to resign, and Ethiopia introduced a state of emergency for the second time in two years.
A new prime minister is expected to be installed by the ruling coalition in the coming days.
Ethiopia is one of Africa’s most prominent economies, Africa’s second most populous country and a key security ally of the West but is often accused by rights groups and opposition groups of stifling dissent and arresting opposition party members, journalists, activists and bloggers.
Copyright © 2018 The Associated Press. All rights reserved. This material may not be published, broadcast, written or redistributed

søndag 25. mars 2018

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy Press Release

Patriotic Ginbot 7 movement for unity and democracyPatriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy would like to extend its heartfelt gratitude to Majority Leader Kevin McCarthy for scheduling H.Res 128 for the House vote on April 9, 2018. We would also like to thank Rep. Christopher Smith, Chairman of the House subcommittee on Africa for sponsoring H.Res 128 “Supporting respect for human rights and encouraging inclusive governance in Ethiopia”. Our thanks also go to Ranking Member Karen Bass and ALL the co-sponsors of the resolution.
We would like to specially thank Rep. Mike Coffman (R-CO) for his hard work and tireless effort on behalf of his Ethiopian-American constituency who brought us to this point. Ethiopian-Americans across this great land and Ethiopians at home are truly indebted to Rep. Mike Coffman of Colorado.
We strongly believe that the passage of H.Res 128 will send a strong message to the Ethiopian regime that has declared a draconian State of Emergency (SoE) for the second time in two years. The SoE has put the country under a military control inflaming the political crisis that will most certainly lead Ethiopia and the region into prolonged instability unless the Ethiopian regime is forced to terminate the SoE and seek a political solution for the crisis and the future of the country with all stakeholders.
Ethiopians abroad demand that Human Rights is respected in Ethiopia. House Resolution 128 will also give moral support to the Ethiopian people who are single-mindedly determined to transition Ethiopia from dictatorship to democracy and peace in order to have their full say in how their country is governed. We strongly believe that H.Res 128 will be an affirmation of the strong historical ties between Ethiopia and the United States established over one hundred years ago by President Teddy Roosevelt.
As the most populous regional power in the Horn of Africa, Ethiopia will always remain a strong ally of the United States sharing the common objective of peace, stability and economic development in Ethiopia and in the geopolitically strategic Horn of Africa

fredag 23. mars 2018

በወሮበሎች አዚም የባዘንን አንሁን! (ሰርፀ ደስታ – የሳተናው አምደኛ)

ሰሞኑን ወንበዴው ወያኔ የሽብር አዋጅ አውጥታ ማንም ሰው ምንም ነገር መናገር አይችልም ብላ ሁሉንም ዝም በማድረግ የራሷን  የውንብድና ወሬ በሰፊው መንዛት ተያይዛለች፡፡ በዚሁ አጋጣሚ የክት የውንብድናና አረመኔነነት አጋሮቿን ከሞቱበት እያስነሳች ለውንብድናዋ እየተጠቀመች ነው፡፡ አሁን ላይ አብዳለች ወያኔ በምንም መልኩ ከአሸባሪነትና አረመኔነት በቀር አንደም አቅም እንደሌላት ሕዝብ ግልጽ ብሎለታል፡፡ አሁን ለሕዝብ አደጋ እየሆነ ያለው ግን በወያኔ የወሮበላ አስተሳሰብ እየተደናበረ የወያኔ ወሬ አናፋሽ የሆነው ተማርኩ የሚለው ጅላጅል ትውልድ ነው፡፡ ሰሞኑን ነጠቃ መንግስት ብላ ወሬ ጀምራለች፡፡ እድሜ ከሰጣት እንዲሁ የተጃጃለ ትውልድ 27 ዓመት  በመተቱም በሽብሩም ያደነዘዘችው ትውልድ ዛሬም ወያኔን እንደ ልዩ ነገር ያያታል፡፡ የወያኔና አጋሮቿን ኢሕአዴግ ብላ የሰራችው ቡድን በአጠቃላይ መንግስት ብሎ መናገር በራሱ እጅግ መዝቀጥ ነው፡፡ መንግስት አምባ ገነን ሊሆን ይችላል ግን መንግስት ጉልበተኛ ነው እንጂ ወሮ በላ አይደለም፡፡  ወያኔ በኢትዮጵያ ምድር 27ዓመት በገዥነት ሥም መኖር መቻሏ ዋና አቅም የሆናት ሕዝብን ከሕዝብ መለያየት መቻሏ ነበር፡፡ ይን ደግሞ ብቻዋን አልነበረም ኦነግ የተባለ ሌላ አረመኔና ወንበዴ አጋሯ ነበር፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያ ለገባችበት ምስቅልቅል ሁሉ ወያኔና ኦነግ በአንድነት ቆመው አገርን ለማፍረስ ሕዝብን ለመለያየት የቻሉትን ሁሉ አደርገዋል፡፡ አሁንም ሁለቱም በዚሁ አላማቸው ጸንተው ቆመዋል፡፡ ሰሞኑን ኦነግ የትግል አጋር ነኝ በሚል የሕዝብን ትግል በውጭ ኃይል እየተጋዘ በአገር ላይ የተነሳ ለማስመሰል ለወያኔ ለዘመናት የተጠቀመችበትን ማጃጀላ ዛሬም ለመጠቀም ይረዳት ዘንድ ምልክት ለመሆን ነበር የኦነግ የትግል አካል ነኝ ማለት ምክነያቱ፡፡ ኦነግ ኢትዮጵያ ምድር ላይ አንደም ቦታ እንደሌለ እኛ እናውቃለን፡፡ ወያኔ አንተ እንዲ በል እኔ ደግሞ በኤርትራ የሚደገፍ ቄሮ በማለት የወሬ አዚም እየነዛሁ እጨፈጭፈዋለሁ ነው፡፡ የወያኔና ኦነግ ዘላለማዊ ቃልኪዳን ይሄና ይሄ ብቻ ነው፡፡ ይህ ከአልገባን ዛሬም ገና ነን፡፡ ኦነግ በኦሮሚያ ክልል ኦሮሞን ኢላማ ለማድረግ ነው፡፡ በተመሳሳይ ግንቦት 7 የተባለው ድርጅት አማራን ኢላማ ለማድረግ ከወያኔ ጋር ውል እንደገባ ካልገባን ችግሩ ከወያኔ ሳይሆን ከራሳችን ነው፡፡ ግንቦት 7 እያደረገ ያው ኦነግ በኦሮሚያ እንደሚያደርገው ነው፡፡ ልብ በሉ አማራ እስከ ብዙ ዘመን ተገዳይ እንጂ መብትም ጠያቂ አልነበረም፡፡ አማራ ወያኔን የማስጋት እድል እየተፈጠረ ሲመጣ ግንቦት 7 የሚባል የኦነግ ተመሳሳይ ሥም አማራን ኢላማ ለማድረግ ዋና ምክነያት ሆነ፡፡ ሁለቱም በኤርትራ በኩል ነው እየታገልን ነው የሚሉት፡፡ ኤርትራ የኢትዮጵ ጠላት ተደርጋ ታይታለች፡፡ ይታያችሁ የኤርትራ ሕዝብ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት መሆኑ ነው፡፡ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖች ያለቁበት የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ሳይቀር ግን የሻቢያና ወያኔ ቁማር ድራማ እንደሆነ አውቀናል፡፡ ኢሳያስን ያዳነው መለስ ነው እኮ ሊያውም ኢትዮጵያውያን ወታደሮች እንዲያልቁ በማድረግ፡፡ እዚህ ቁማር ውስጥ ዛሬ በአጋርነት እየተጫወቱ ያሉት ኦነግና ግንቦት7፡፡ ኦነግም ሆነ ግንቦት7 የሚባል የታጠቀ ኃይል እንደሌለማ ከወያኔ በላይ የሚያውቅ የለም፡፡ ሲጀምር ኦነግና ግንቦት7 የሚንቀሳቀሱት በወያኔ እቅድ ነው፡፡ ደምህት የተባለ የታጠቀ ቡድን አለ፡፡ ይሄ ግን ወያኔ አንድ ነገር ብትሆን ተጠባባቂ ሆኖ ታጥቆ የሚጠብቅ እንጂ ወያኔን ሊዋጋ አደለም፡፡ ልብ በሉ ሻቢያ ደምህትን እንደ መነሻ አድርጋ ወያኔ አንድ ነገር ቢሆን ከኋላ ለመታደግ ነው፡፡ ሻቢያና ወያኔ እንዲህ ነው እየቆመሩብን ያለው፡፡ ይህን አንረዳም፡፡
ወያኔ ሰሞኑን ብቻዋን ወሬዋን እየነዛች ነው፡፡ ይሄን እየያዘ አዳሜ አብሮ ሽብር ነዥ ሆኖ እናየዋለን፡፡ እውነታው ግን የወያኔ ጀምበር እየጠለቀች መሆኑ ብቻ ነው፡፡ አይቀሬ የሆነው የወንብዴው ቡድን መሸነፍ ብቻም ሳይሆን እይሆኑ ሆኖ እንዲያበቃ እንጂ አሁንም አልቆላታል፡፡ ለማና ገዱ መናገር አልቻሉምና ለማና ገዱ እጅ ሰጡ አይነት ወሬ በሰፊው ይዛዋለች፡፡ ምድረ ዲያስፖራ በዚህ የወንበዴ ወሬ ሲፍረከረኩ ታይተዋል፡፡ እርግጥ ነው ዲያስፖራ ተብዬው ብዙው አጋጣሚውንም እንደመነገጃ ስለሚጠቀመው የወንበዴውን ውዥንበር ማባዛት ሥራው ነው፡፡ ዛሬም የኦነግ ባንዲራ በኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል አጋርነት ሥም በየአገራቱ አብሮ ሲያውለበልብ የሚታይ የባዘነ ዲያስፖራ ነው፡፡ ለመሆኑ ግን ኦነግን ለማስተዋወቅ ነው ወይስ ሰላማዊ ሰልፍ ነው?
ትንተና እንሰጣለን ብላችሁ የምትቀዣብሩ ከአልገባችሁ ዝም በሉ፡፡ ሆን ብላችሁ ከሆነ ግን ሥራችሁ ነው፡፡ የሕዝብን ትግል ለማፋጠን አንድ ደረጃ ከፍ የሚል እርምጃ ለመውሰድ እየተዘጋጀን ነው፡፡ ለ27ዓመት የወንበዴ ቅጥረኛ ሆኖ ሲያገለግል የኖረ የታጠቀ የኦሮሞ፣ አማራና ሌሎች የታጠቀ ኃይል ሁሉ ከሕዝቡና ዳረጎት እየሰጠ ከሚያኖረው ወንበዴ ቡድን እንዲመርጥ ልናሳስበው ይገባል፡፡ ኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ሳይኖራት 27ዓመት ሞላ፡፡ የደርግ እየተባለ የሚጠራው ሰራዊት እኮ የኢትዮጵያ ነበር፡፡ ይህን ብረሀነመስቀል አበበ ሰኚ በቅርቡ ቪኦኤ ይህን እውነት ጥሩ አድርጎ ገልጦታል፡፡ አሁን ያለው ወታደር የወያኔ ቅጥር እንጂ የኢትዮጵያ አደለም፡፡ በደርግ ጊዜ የነበረው ወታደር ታሪኩ ከንጉሱ የቀጠለ ነው እንጂ ደርግ የፈጠረው አደለም፡፡ ዛሬ አገር እንዲሀ በአለ ምስቅልቀል ገብታ ሊታደግ የሚችል ሠራዊት የጠፋው ምክነያቱ፣ በኢትዮጵያ ሠራዊትነት የሚጠራው የዛሬው የታጠቀ ኃይል በግልጽ የወንበዴው ወሮ በላ ቡድን የግል ቅጥር ነው፡፡ ይህን እውነት እንዲያስተውል በሰራዊትነት ተቀጥሮ ላሉት ሁሉ በተቻለን ሁሉ በማድረስ ወንበዴዎቹን እንዲበቀል ማድረግ ዋነኛ አላማችን ሊሆን ይገባል፡፡ ትግሬዎች አሁንም ጥሪ እየቀረበላቸው ቢሆንም ትግሬና ወያኔ እንድ ነው የተባለውን ብሂል ይበልጥ እያረጋገጡልን ይመስላል፡፡አዝናለሁ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብን እጅግ ተፈታትናችሁታል፡፡ እስካሁን ከልብ ሆኖ ወያኔን ሲቃወሙ ያየኋቸው ጥቂት ትግሬዎች ናቸው፡፡ መቃወሙ ቀርቶ ግን ሕሊና የሚያሳድፍ ነገር መናገርን ቢያቆሙ ለእነሱ እየመጣባቸው ያለውን አደጋ በአቀለላቸው ነበር፡፡ አዝናለሁ፡፡ ዛሬ ለብዙ ኢትዮጵያዊ ትግሬ የሆነው ድሮ ሰው የሚየስበው ሀይማኖተኛ፣ መልካም ህዝብ ምናምን የሚባለው ሳይሆን ፍጹም እምነት የሌለው አረመኔና ነውር የለሽ ስግብግብ ነው፡፡ አዝናለሁ፡፡ ይህን እውነት መናገር ስላለብኝ ነው፡፡
ሚዲያዎች የኢትዮጵያን ሕዝብ ትግል ያግዛሉ ብለን ብንጠብቅ ብንጠብቅ ምንም የለም፡፡ ቪኦኤና ዶቸቬሌ፣ ኤስ ቢኤስ ባይኖሩ የሕዝብ አይንና ጆሮ ነን የሚሉት እንደነ ኢሳት ያሉ በወያኔ የውዥንበር ወሬ የበለጠ ባባዘኑን፡፡ ሰሞኑን ኢሳት ግንቦተ7 በዚህ ቦታ እንዲህ አደረገ እንዲህ ሊያደርግ ነው የቀበሌ እስር ቤት ሰበረ ምናምን ወሬ ዋና ጉዳዩ ሆኖ ነው የሰነበተው፡፡ ይታያችሁ አሁን ማን ይሙት ወያኔን ለመጣል አፋፍ ላይ እየታገለ ላለ ሕዝብ ይሄ ተራ የወያኔ አጋር የሆነው ግንቦት 7 ወሬን መስማት የሚፈልግ አለ? ሌላው በኦሮሞ ሥም ሌላ ቲቪ ተከፍቷል ኦሮሚያ ቲቪ የሚል ይሄ ደግሞ የኦነግን ወሬ ነው የሚነዛው፡፡ ሁሉም ለወያኔ ግብዓት የሚሆን ፕሮፓጋንዳ ነው የሚነዙት፡፡ ማስተዋል ከሌላ ምን ይደረጋል፡፡
ሌላው ውዥንብር እምነትን አስመልክቶ ነው፡፡ መቼም በወሮበላው ወያኔ ዋና የወሮበላ መከማቻ ከሆኑት ዋነኛዎቹ ቤተ እምነቶች ናቸው፡፡ አሁን ችግር የለም ሀዋሪያ ነብይ ምናምን ሆኖ እንደልብ እየዘባረቁ ሕዝብን ማደንዘዝ ነው፡፡ ወያኔ የምትፈልገው ይሄንን ነው፡፡ በጽኑ እምነት ላይ ቆሞ አገርና ሕዝብን የሚያስብ ትውልድን ለማጥፋት ይሄ እንዱ የወሮበላው ቡድን ሥልት ነው፡፡ አገሪቱ በጠንቋዮች ተወራለች ቢባል ይሻላል፡፡ በዚህ ጉዳይ በትልልቅ የሕዝብና አገር ጉዳዮች ሲሳተፉ ያየናቸው ሳይቀሩ ቀስ ብለው ተራ ሀይማኖታዊ ያልሆነ ሰባኪዎች ሆነውልናል፡፡ ሐይማኖት ፍልስፍና ነው፡፡ ፍለስፍናው ደግሞ ከሁሉም የረቀቀ ነው፡፡ ማንም እየተነሳ ነብይ ሀዋሪያ ነኝ እንደሚለው አደለም፡፡ ኢትዮጵያ ለዘመናት በጠላት አልደፈር ያለችው በጽኑ እምነት ላይ በቆሙ አባቶቻችንና እናቶቻችን የሆነውን ያህል ዛሬ አገርና ሕዝብን የሚሸጡና የሚያመክኑ የሰይጣን መንፈስ የሰፈረባቸው አገሪቱን ወረዋታል፡፡
ትኩረት እንዳይኖረን ብዙ እየተረባረቡ ነው፡፡ እነሱ አያፍሩም እኛ ግን ወራዶችን ወራዳ ለማለት እናፍራለን፡፡ በቃ አካፋን አካፋ ዶማን ዶማ ማለት ተገቢ ነው፡፡ ፊት መስጠት አያስፈልግም፡፡ ወራዶችን ማክበር በወራዳ ሥራቸው መተባበር ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ንቁ፡፡ ወያኔ አሁን አብዳለች፡፡ አንዴ የወያኔ መሪዎችን ኢላማ ያደረገ ጥቃት እስኪጀመር ነው፡፡ ይህ ደግሞ በቅርብ ይሆናል፡፡ በዛው ልክ ሕዝብን ከሕዝብ አንድ የማድረግ ሥራ ይሰራ፡፡ ይሄ ኢሳት የሚባለው የግንቦት 7 ልሳን በሕዝብ ገንዘብ ከሚቀልድ ሚዲያውን ለሕዝብ አገልግሎት ማዋል ነው፡፡ ሚዲያዎች ህዝብን በመረጃ ለማነጽም ሆነ አመራር ለመስጠት ወሳኝ ናቸው፡፡ ኦኤም ኤን ተመክሮ ይሁን ሁኔታውን ለመጠቀም ብዙ መሻሻል ይታይበታል፡፡ ግን ገና ብዙ ይቀረዋል፡፡ ብዙ ጸረ ኢትዮጵያ የሆኑ ዛሬ የኢትዮጵያ ጉዳይ እያሳሰባቸው ነው፡፡ ከመጀመሪያውም ተናግሬ ነበር፡፡ ማንም ኢትዮጵያዊ ከኢትዮጵያዊነት በታች ኢትዮጵያ ውስጥ የመኖር እድሉ አደጋ ላይ፡፡ ኦሮሞ፣ ኦሮሞ፣ እያሉ የኦሮሞን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊነት አምክነው ለወያኔ የጣሉት ከወያኔ ጋር ኦሮሞ ነን ባዮች ናቸው፡፡ ወያኔ ይህ ስለተሳካላት 27 እድል አገኘች፡፡ ኦሮሞ ኢትዮጵያነት ከእኔ በላይ ማለት ሲጀምር በፍርሀት መናድ ጀመረች፡፡ ሚስጢሩ ይሄው ነው፡፡ ባንዳን አገር ዋዳዶች ያስፈሯታል፡፡ አሁንም ግን ገና ነው፡፡ የአባቶቻችንን አጥንትና ደም ነው የተሳለቅንበት፡፡ ኢትዮጵያዊነት በደምና አጥንት የኖረ ነው ስንል መሳለቂያ ሆኗል፡፡ አገርን የገነቡ ከጠላት ጠብቀው ለትውልድ ያኖሩ ጀግኖች በወራዶች አፍ ተሰደቡ፡፡ ሚኒሊክና ጎበና የወራዶች አፍ ማሟሻ ሆኑ፡፡ ወሮበሎች ከበሩ፡፡ ከሚኒሊክ ጀምሮ በጦር ትምህርት ቤትነት የሚታወቀው ሆለታ ጦር ትምርት ቤት ሥሙ ተቀይሮ በወንበዴ ሥም ተሰየመ፡፡ ኃይሎም አርዓያ የሚባል ወንበዴ እንጂ ኢትዮጵያ ኃይሎም አርዓያ የሚባል ጀግና ኖሯት አያውቅም፡፡ መለስ ዜናዊ የተባለው ወንበዴ ሲሞት ጭራሽ እንዲመለክላቸው ፈለጉ፡፡ የመለስ ፓርክ በሚል ቀበሌ ሳይቀር የጣዖት ስፍራ አኖረች፡፡ የሆነውና እየሆነ ያለው ሁሉ እንዲህ ነው፡፡
ኢትዮጵያውያን ሁሉ በነገሮች አትባዝኑ፡፡ ትኩረታችሁን ሁሉ ይሄን ወሮበላ ቡድን ከምድረ ገጽ ማጥፋት ላይ ይሁን፡፡ ልዑል እግዚአብሔር ይረዳናል፡፡ እኛ ግን ከልብ መቆም አለብን!
ልዑል እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይጠብቅ! አሜን!

Ethiopia police fail to produce detained blogger who criticized martial law

Ethiopan blogger Seyoum Teshome is seen in an undatd photo.
Ethiopan blogger Seyoum Teshome is seen in an undatd photo.
(Africa News) — A university lecturer and prominent blogger in Ethiopia, Teshome Seyoum, was due to appear in court on Thursday (March 22) but the police failed to produce him, local media and rights group reported.
The Addis Standard portal quoted his family members as saying prison authorities said he could not appear in court because ‘he was detained under the state of emergency.’
Teshome, who publishes theEthiothinktank blog, was reportedly picked up by security forces on Thursday (March 8) at his home near the Woliso campus of Ambo University, where he lectures, witnesses told the Voice of America and Deutsche Welle news outlets.
He was put before court in the capital Addis Ababa and the judge gave police fourteen days to establish a case against him.
The reason for his arrest is because he had criticised government’s decision to impose a state of emergency on February 16, barely twenty-four hours after Prime Minister Hailemariam Desalegn resigned his position. Government said the move was to curb rising insecurity nationwide.
According to Robert Mahoney of deputy executive director of Committee to Protect Journalists (CPJ) Ethiopian authorities are hiding behind the SOE cloak to stifle critical voices like Seyoum, adding that they have often failed to follow due process in detaining such voices.
“Ethiopia cannot again use the cloak of a national emergency to round up journalists and stifle critical voices,” Mahoney said in a CPJ statement reacting to Seyoum’s arrest.
“This is the second time that authorities ignored due process to detain Seyoum Teshome. He should be released immediately and unconditionally,” Mahoney added.
He is held at the Maekelawi prisons located in Addis Ababa. The facility notorious for its use of torture according to several human rights groups and former detainees is earmarked for closure, as part of political reforms announced in January this year.
PM Desalegn is still holding on to his position temporarily as the ruling coalition’s council meets to elect his successor.

mandag 12. mars 2018

ሞያሌ ዉስጥ በሠላማዊ ዜጎች ላይ ለተፈጸመው ጭፍጨፋ ተጠያቂዉ ህወሓትና ኮማንድ ፖስቱ ናቸው! – (ከአርበኞች ግንቦት 7 የተሰጠ መግለጫ)

የኢትዮጵያ ህዝብ እያካሄደ ያለውን የፍትህና የእኩልነት ጥያቄ ለማፈን ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠረው የራሱ ፓርላማ ሳይቀር እየተቃወመው በጉልበት አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በህዝባችን ላይ የጫነው እብሪተኛው
የህወሃት አመራር በሞያሌ ከተማ ያሰማራው ነፍሰ ገዳይ የአጋዚ ጦር ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ መጋቢት 1 ቀን 2010 ዓም በሞያሌ ከተማ ሠላማዊ ዜጎች ላይ የሚዘገንን ጭፍጨፋ በመፈጸም በርካታ ሠለማዊ ዜጎችን ገድሏል።
ይህንን ጭፍጨፋ አስመልክቶ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈጸም የተቋቋመው የኮማንድ ፖስት በትናንትናው ዕለት መጋቢት 2 ቀን 2010 አ.ም ባወጣው መግለጫ ጭፍጨፋውን ያካሄደው የሠራዊት ክፍል “የኦነግ ሠራዊት በከተማው ገብቷል” የሚል የተሳሳተ መረጃ ተቀብሎ እንደሆነና 9 ሠላማዊ ዜጎች ውድ ህይወታቸውን እንዳጡ፤ 12 የሚሆኑት ደግሞ ቆስለው ሆስፒታል እንደገቡ አረጋግጧል። ጥቃቱ ሲፈጸም የተመለከቱ የከተማው ነዋሪዎች በበኩላቸው የሟቾች ቁጥር 17 መድረሱንና ከፍተኛ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸው ወደ ሆስፒታል የተወሰዱና ነፍሳቸው በሞትና በህይወት መካከል እያጣጣረች በመሰቃየት ላይ የሚገኙ ከሟቾች ቁጥር በእጥፍ እንደሚበልጡ እየተናገሩ ነው።
ህወሃት በአገዛዝ ዘመኑ እንዲህ አይነት የጅምላ ጭፍጨፋ በሠላማዊ ዜጎች ላይ ሲፈጽም የመጀመሪያው ጊዜ እንዳልሆነ ህዝባችን በሚገባ ያውቃል። መሪዎቹ ገና የበረሃ ትግል ላይ በነበሩበት ወቅት የፖለቲካ አላማቸውን የተቃወሙ ቁጥራቸው ከሠላሳ ሺህ በላይ የሆኑ የትግራይ ተወላጆችን አንድ በአንድ እየረሸኑ የመጡ መሆናቸውን ታሪክ በማይደበዝዘው ብዕሩ መዝግቦታል። በለስ ቀንቷቸው ሥልጣን ላይ ከወጡም ቦኋላ በመጀመሪያዎቹ የሥልጣን ዘመናቸው አማራውንና ኦሮሞውን ለማጨራረስ በበደኖ፤ በአርባ ጉጉ ፤ በወተር፤ በአረካ ፤ በአሰላ ሠራዊታቸውን በማዝመት በርካታ ሠላማዊ ዜጎችን በአሰቃቂ ሁኔታ አስገድለዋል። ከዚያም በኋላ በሃዋሳ፤ በጋምቤላ ፤ በኦጋዴን ፤ በአዲስ አበባ፤ በባህርዳር ፤ በጎንደር ፤እና በተለያዩ የኦሮሚያና የአማራ ክልሎች ተመሳሳይ ጭፍጨፋ ሲፈጽሙ ኖረዋል። በነዚህ ሁሉ ጭፍጨፋዎች፤ የሃብት ዘረፋና አድሎአዊ አሠራር የተማረረው ህዝባችን በሠላማዊ መንገድ ተቃውሞውን በብዛት መግለጽ ከጀመረበት ካለፉት ሶስት አመታት ወዲህም በተለያዩ የኦሮሚያና አማራ ከተሞች ከሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች በየአደባባዩ ተጨፍጭፈዋል። መንፈሳዊና ባህላዊ በዓላትን ለማክበር የወጡ ዜጎች ሳይቀሩ ከዓመት በፊት በቢሾፍቱ የኢሬቻ በዓል ላይ፤ ከሁለት ወራት በፊት ደግሞ የጥምቀት በዓል ለማክበር በወጣው የወልዲያና አካባቢው ነዋሪዎች ላይ ዘግናኝ የሆነ ተመሳሳይ ጭፍጨፋ ተፈጽሟል። አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከታወጀ ካለፈው ሶስት ሳምንታት ወዲህም በአምቦ፤ በጉደር ፤ በወሊሶ ፤ በሱሉልታ፤ በለገጣፎ ፤ በጂማ ፤ በወልቂጤ ፤ በመቱ ፤ በነቀምቴ ፤ በጊምቢ ፤ በመንዲ ፤ በደምቢዶሎ፤ በምሥራቅ ሃረርጌ ወዘተ ቁጥራቸው በግልጽ ያልታወቀ በርካታ ንጹሃን ዜጎች በተመሳሳይ ጭካኔ ተገድለዋል። በብዙ ሺ የሚቆጠሩት ደግሞ ወደ እሥር ቤት ተግዘዋል።
ከትናንት በስቲያ በሞያሌ ከተማ ነዋሪዎች ላይ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ በቅርብ ጊዜያት ከተፈጸሙት ተመሳሳይ ጭፍጨፋዎች ልዩ የሚያደርገው አገዛዙ የተለመደውን የጭካኔ እርምጃውን ለመውሰድ ምንም አይነት ምክንያት ሳይኖረውና በከተማው ውስጥም ሆነ በአካባቢው ምንም አይነት እንቅስቃሴ በለሌበት ሰዓትና ቀን ሰዎች በብዛት በሚኖርበት የከተማው ጎዳና ላይ በሚንቀሳቀሱትና በተኩሱ ተደናግጠው የንግድ መደብሮቻቸውን በዘጉት ዜጎች ላይ ቤቶቻቸውን በርግዶ በመግባት የተፈጸመ የሽብር እርማጃ መሆኑ ነው ። ለዚህም የተሰጠው ምክንያት “የኦነግ ታጣቂዎች ከተማ ውስጥ ገብተዋል” የሚል የተሳሳተ መረጃ ነው ተብሏል። የኦነግ ሠራዊት ከተማ ውስጥ ገብቶ እንኳ ቢሆን ምንም አይነት መሣሪያ ያልታጠቁ ዜጎች በጥርጣሬ በተገኙበት እንዲገደሉ የሚፈቅድ ህግም ሆነ አሠራር የለም። በዚህም የተነሳ ይመስላል ጭፍጨፋው እንዲካሄድ ሠራዊት አስታጥቀው በመላው አገሪቱ ያዘመቱት የህወሃት መሪዎችና የኮማንድ ፖስቱ ከህዝብ የሚቀሰቀስባቸውን ቁጣ ለማለዘብና ከአለም አቀፍ ማህበረሰብ በተለይም ከምዕራባዊያን ወዳጆቻቸው ሊሰነዘርባቸው የሚችለውን ውግዘት ለማስቆም ፈጥነው የሽብር ጥቃቱን ታዘው በፈጸሙት 5 የሠራዊቱ አባላት ላይ በማላከክ “ተጠያቂዎቹን ለህግ ለማቅረብ ምርመራ ጀምረናል” የሚል መግለጫ ያወጡት። ከእስከ ዛሬው ልምድ ህወሃት አልሞ ተኳሾቹን በአብዛኛው የአገራችን ማህበረሰብ ላይ በማዝመት ሲፈጽማቸው ለኖረው ጭፍጨፋ አንዳችም ጊዜ ተጠያቂ የሆነ ሰው ህግ ፊት አቅርቦ እንደማያውቅ ጠንቅቆ የሚያውቀው የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ ምዕራባዊያን ወዳጆቹ በዚህ የኮማንድ ፖስት መግለጫ ሊደለሉ ይችላሉ ብሎ አይታሰብም።
ይልቁንም ከዚህ መግለጫ መማር የተቻለው ከበላይ አለቆቹ ትዕዛዝ በመቀበል በገዛ ወገኑ ላይ ጭፍጨፋና ሰቆቃ እያደረሰ ያለው ተራው የመከላኪያ ሠራዊት አባላትና የበታች መኮንኖች ለሚፈጽሙት ለያንዳንዱ ጭፍጨፋ ተጠያቂነት ሲመጣ ሃላፊነት ሊወስድላቸው የሚችል አንዳችም የህወሃት ወይም የኮማንድ ፖስት አመራር እንደሌለ ግልጽ መሆኑ ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 በሞያሌ ንጹሃን ዜጎች ላይ የተወሰደውን ይህንን ጭፍጨፋ በጥብቅ እያወገዘ ለዚህ ተጠያቂዎቹ የሽብር ጥቃቱን ከፈጸሙ የሠራዊቱ አባላት በተጨማሪ ይህንን የሽብር እርምጃ በወገን ላይ እንዲወሰድ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ ሠራዊቱን በከተማው ያሰፈረው የኮማንድ ፖስትና ከኮማንድ ፖስቱ በስተጀርባ ያለው የህወሃት አመራር መሆናቸውን ያስታውቃል።
ለሃብት ዘረፋ ምንጭ ያደረጉትን የመንግሥት ሥልጣን ዕድሜ ለማራዘም ሲሉ በሠላማዊ ዜጎቻችን ላይ እንዲህ አይነት የጭፍጨፋ እርምጃ እያስወሰዱ ያሉት የኮማንድ ፖስቱና የህወሃት አመራሮችን ለህግ ለማቅረብም ንቅናቄያችን አርበኞች ግንቦት 7 ከሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሆኖ አስፈላጊውን ሁሉ ትግል ማካሄዱን በጽናት ይቀጥላል።
ህወሃት በሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ እንዲህ አይነት ጭፍጨፋ፤ እስርና እንግልት መቆሚያ እንደማይኖረው ያለፈው 27 ዓመታት ተሞክሯችን በቂ ትምህርት ሰጥቶናል። በመሆኑም ይህንን ጭፍጨፋ ለማስቆም የሚቻለው በሁሉም የአገራችን ክፍል የሚኖረው ህዝባችን በኦሮሚያና በአማራ አካባቢ እየተካሄደ ያለውን ህዝባዊ ተቃውሞ በመቀላቀል የህወሃትን አገዛዝ ፍጻሜ ለማምጣት በጋራ ስንንቀሳቀስ እና የህግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት በአገራችን ሲመሰረት ብቻ መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 መላውን ህዝባችንን ማስታወስ ይወዳል።
በመከላኪያ ሠራዊት፤ በፖሊስና የጸጥታ ጥበቃ ተቋማት ውስጥ ያላችሁ ወገኖች !
በአለቆቻችሁ ትዕዛዝ በማንኛውም ዜጋ ላይ ለምትፈጽሙት ግድያ ፤ እስርና ሰቆቃ በህግ የተጠያቂነት ጊዜ ሲመጣ “አለቆቼ አዘውኝ ነው” በማለት ከተጠያቂነት ነጻ መውጣት እንደማይቻል በዓለም አቀፍ ህግ ካለው ድንጋጌ በተጨማሪ በሞያሌ ላይ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ ወንጀል በናንተ ላይ ለማላከክ አገዛዙ ከሰጠው መግለጫ ትምህርት ልትቀስሙ ይገባል። ስለዚህ ህዝብ አንቅሮ የተፋው ይህ የህወሃት አገዛዝ እናንተን እንደመሣሪያ ተጠቅሞ የሥልጣን ዕድሜውን ለማራዘም የሚያደርገውን ማንኛውንም ሙከራ ለማስፈጸም የሚሠጣችሁን ትዕዛዝ እንቀበልም በማለት ህዝባዊ ወገናዊነታችሁን እንድታሳዩና ከለውጥ ፈላጊው ማህበረሰባችሁ ጎን እንድትሰለፉ አርበኞች ግንቦት 7 ወገናዊ ጥሪውን ያቀርብላችኋል።
በህወሃት ነፍሰ ገዳዮች ጥይት ህይወታቸውን ላጡ ሰማዕታት ቤተሰቦች ፤ ወዳጅ ዘመዶች ሁሉ አርበኞች ግንቦት7 መጽናናቱን ይመኛል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !
አርበኞች ግንቦት 7
መጋቢት 3/ 2010 ዓም

fredag 23. februar 2018

Ethiopia: New State of Emergency Risks Renewed Abuses

Overbroad, Vague Provisions Undercut Rights
Police officers patrol along a road in Addis Ababa.
Police officers patrol along a road in Addis Ababa, Ethiopia, February 21, 2018. © 2018 Reuters
(Human Rights Watch) — Ethiopia’s newly proclaimed state of emergency risks further closing the space for peaceful political activity, Human Rights Watch said today. The action dashed hopes that the release of key political prisoners days earlier was a first step toward more widespread political reforms. The government should promptly repeal or revise restrictions that violate the rights to freedom of peaceful assembly, association, and expression protected under international human rights law.
On February 17, 2018, following Prime Minister Hailemariam Desalegn’s resignation, Defense Minister Siraj Fegessa announced a countrywide six-month state of emergency. The Directive of the State of Emergency contains overly broad restrictions and vague language that will facilitate government abuses, Human Rights Watch said. During Ethiopia’s previous countrywide state of emergency, from October 2016 until August 2017, security forces arrested more than 20,000 people and committed widespread rights violations.
“Ethiopia’s new state of emergency threatens to block the peaceful expression of views on critical issues facing the country,” said Felix Horne, senior Africa researcher at Human Rights Watch. “Banning public protest and handing the army sweeping new powers to crack down on demonstrators, media and political parties violates rights and crushes the potential for meaningful dialogue on the way forward.”
The directive bans all protests without permission of the Command Post, a body led by the prime minister to manage the state of emergency. A blanket ban on protests is an overly broad restriction on the right to peaceful assembly, including during a state of emergency. If any criminal acts are committed during a protest, the authorities can prosecute them under Ethiopian law.
The directive also broadly forbids disseminating any information deemed critical of the state of emergency. The Command Post is empowered to “close any media to safeguard the constitution,” the government’s news agency said.  And regional government media outlets are prohibited from commenting on the state of emergency without Command Post permission. These measures pose a serious threat to Ethiopia’s media and expanding social media community, and place at risk Ethiopians who benefit from the media in the Ethiopian diaspora.
Much of the language in the directive is vague, with many terms undefined, including restrictions on “communicating with anti-peace groups,” or any acts that “disrupt tolerance and unity.” Given the government’s lengthy history of conflating peaceful expressions of dissent with criminal activity, the vague provisions provide Ethiopia’s abusive security forces with seemingly unfettered power to determine state-of-emergency violations.
Other problematic provisions give security forces standing permission to enter schools and universities to “arrest and stop mobs,” to search houses without a warrant, and to ban various forms of peaceful protest including stay-at-home strikes, closing shops, and blocking roads.
Anyone found violating the state of emergency is subject to arrest without warrant by the Command Post to face charges or be compelled to undergo “rehabilitation”- a euphemism for detention without charge often involving abusive treatment and political indoctrination. Torture and other ill-treatment in detention remain serious problems in Ethiopia.
Under the International Covenant on Civil and Political Rights (ICCPR), which Ethiopia ratified in 1993, during a state of emergency a government may only derogate, or suspend, certain rights “to the extent strictly required by the exigencies of the situation.” These measures must be of an exceptional and temporary nature. Other rights, such as the right to life and freedom from enforced disappearance, torture and ill-treatment, may never be suspended. Under the African Charter on Human and Peoples’ Rights, no derogation of charter rights is allowed during a time of emergency.
The United Nations Human Rights Committee, the international expert body that monitors compliance with the ICCPR, has stated that governments need to “provide careful justification not only for their decision to proclaim a state of emergency but also for any specific measures based on such a proclamation.”
Ethiopia’s constitution permits the government to impose a state of emergency following a foreign invasion or due to the “breakdown of law and order which endangers the Constitutional order and which cannot be controlled by the regular law enforcement.”  While there were sporadic protests and incidents of unrest in the week prior to the announcement, Human Rights Watch knows of no  evidence of a breakdown of law and order that could not be handled through regular law enforcement. A day before the state of emergency was announced, the communications minister denied that a state of emergency would be declared because “there are no grounds for it.”
It was not clear how the state of emergency will impact upcoming countrywide local elections scheduled for May. The new restrictions raise serious concerns as to whether candidates, particularly from opposition parties, will be able to fully and freely campaign, Human Rights Watch said.
The government has not addressed most protester grievances amid a growing power struggle among parties within the ruling Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) coalition. Large-scale and mainly peaceful anti-government protests have swept through Oromia, Ethiopia’s largest region, since November 2015, and the Amhara region since July 2016 despite extensive government restrictions on peaceful assembly and expression. Additional clashes over the last year, precipitated by attacks from the Somali regional government’s abusive Liyu police inside Oromia region, resulted in hundreds of deaths and over one million people displaced from both the Oromia and Somali regions.
The United States government, historically a close ally of Ethiopia, issued an unusually critical statement to “strongly disagree” with the declaration of a state of emergency. Other allied governments should follow the US lead and strongly urge restoration of basic rights and the opening up of political space, Human Rights Watch said.
Ethiopia’s constitution requires approval of any state of emergency by two-thirds of the House of Peoples’ Representatives within 15 days of its declaration — by March 4. House members should either vote to reject the state of emergency or ensure that all provisions inconsistent with international law are repealed or substantially revised, Human Rights Watch said.
“Restricting basic rights has led Ethiopia into crisis, and further suppression of rights through a new state of emergency only risks making matters worse,” Horne said. “The government’s use of a state of emergency risks plunging Ethiopia into a greater crisis. The parliament can play an important role in pushing for meaningful reforms, starting with rejecting unlawful restrictions under the state of emergency.”