fredag 6. juli 2018

ሰበር ዜና….ብጹዕ አቡነ ማቲያስ ስልጣናቸውን በሚቀጥሉት ሳምንታት በፈቃዳቸው ሊለቁ ነው

ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ እና ዶ/ር ደብረጽዮን
ባለፈው ሳምንት ሲካሄድ የነበረውና ለአራት ቀናት ያክል የተካሄደው  36ኛውየሰበካ  መንፈሳዊ  ጉባዔ   ላይ ከሌሎች ጳጳሳትና ከቤተክህነት አስተዳደር ጋር በአደባባይ እስጥ አገባ ውስጥ ያሳለፉት አቡነ ማትያስ በጉባዔው ጣልቃ ስልጣናቸውን ለመልቀቅ እንደሚፈልጉ ለቅርብ ሰዎቻቸው ተናግረዋል። በቤተክህነቱ አካባቢ ስልጣናቸውን የሚገዳደሩና የማይታዘዟቸው እየበዙ በመምጣታቸው ክፉኛ የተበሳጩት አቡነ ማቲያስ በመጪው ጊዜ በሚጀምረው የሲኖዶሱ ጉባዔ ላይ መልቀቂያ ማቅረብ እፈልጋለሁ ብለዋል። የፓትርያርኩ እርምጃ ያሳሰበው መንግሥት ፓትርያርኩ ሀገሪቱ ያለችበትን አስቸጋሪ ሁኔታ አጢነው ስልጣን ከመልቀቅ ይልቅ በውይይት ችግሮችን እንዲፈቱ ከማክሰኞ  ምሽት  ጀምሮ አንድ ቡድን በመላክ እያግባባቸው ነው።
አቡነ ማትያስ የቤተክርስቲያኒቱ የወንጌል ማስፋፋትና ትምህርት አንድ አሀድ ከሆነው ማኀበረ ቅዱሳን ጋር የተካረረ ውዝግብ ውስጥ  የቆዩ ሲሆን መንግሥት ማኅበሩን እንዲዘጋው  እስከመጠየቅ ደርሰዋል። ማኀበሩ በቅርቡ የጀመረውን የቴሌቭዥን ስርጭትም   ህገወጥ  በመሆኑ ሊታገድ ይገባል ባይ ናቸው አቡነ ማትያስ።  ፓትርያርኩ  ለአራት ቀናት  በተካሄደው    የመንፈሳዊ ሰበካ ጉባዔ ላይ የማኅበረ ቅዱሳን ተወካዮች እንዳይካፈሉ ትዕዛዝ ሰጥተው ማኅበሩን እንዳይሳተፍ ማድረግ ቢችሉም የቤተክህነት አስተዳደርና ሌሎች ገዳማት የማኅበረ   ቅዱሳንን   ሚና የሚያጎላና የሚያወድስ ሪፖርት ማቅረባቸው አቡነ ማትያስን አስከፍቷቸዋል።
ጉባዔው ማኅበረ ቅዱሳንን ከማውገዝ ይልቅ ለቤተክርስቲያኒቷ አለኝታ የሆነና ድጋፍ  ሊደረግለት  የሚገባ መሆኑንም የተናገሩ አባቶች ነበሩ። በአራቱ ቀን ጉባዔ ከአቡነ ፋኑኤል ጋር የከፋ የቃላት  ልውውጥ ያደረጉት ፓትርያርኩ ብዙውን ጊዜ በዝምታና በማኩረፍ እንዳሳለፉ ከጉባዔው ተሳታፊዎች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የውዝግቡን  መካረር  ተከትሎ መንግሥት የጉባዔውን ሂደት በቅርብ ሲከታተል የቆየ ሲሆን በማጠቃለያ የአቋም መግለጫ ላይ የማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቭዥን ስርጭት “ህገ- ወጥ” መሆኑን የሚገልፅ አንቀፅ ከጉባዔተኛው ስምምነት ውጪ እንዲጨመር መደረጉ ብዙዎችን አሳዝኗል። አንቀፁ የተጨመረው አቡነ ማትያስን “ተሰሚ” አድርጎ ለመሳል “በትዕዛዝ” የተካተተ እንደሆነ ከቃለጉባዔ መዝጋቢዎች ተሰምቷል።
አቡነ ማትያስ
ምንጭ አንድነት ጋዜጣ

ነፃነት ተጎናፅፈናል የብልፅግና ጉዞም ተጀምሯል ለወጡን እንጠብቅ! (ታዬ ደንዳዓ

ለኢትዮጵያ ህዝብ
ለወጡን እንጠብቅ! (ታዬ ደንዳዓ)
እንደ ህዝብ እና እንደ ሀገር ፍላጎታችን ነፃነት እና ብልፅግና ነዉ። ይህ ያልተሳካልን በእርግማን ሳይሆን ከጅቦች አገዛዝ ራሳችንን ማላቀቅ ባለመቻላችን ነዉ። አሁን ነፃነት ተጎናፅፈናል። የብልፅግና ጉዞም ተጀምሯል። ክብር እና ዕድሜ ለዶር አብይ እና ለጓዶቻቸዉ! በሦስት ወር ጊዜ ዉስጥ በጣም ብዙ ለዉጥ አይተናል። በዝህ ፍጥነት በሁለት እና ሦስት ዓመታት በሀገራችን መሠረት ያለዉ ሠላም፣ ዴሞክረሲ እና ልማት ይገነባል። ለዝህ ላበቁን ቄሮዎች፣ ፋኖዎች እና ዘርማዎች ክብር ይገባል።
ጅቦች ግን እያዛጉ ነዉ። ነፃነታችንን አይፈልጉም። የነሱ ብልፅግና በችጋራችን ላይ የተመሠረተ ነዉ። ስለዝህ ለዉጡን ቀልብሰዉ ወደነበርንበት ሊመልሱን እየተሯሯጡ ነዉ። ሩጫቸዉ በሁለት አቅጣጫ ነዉ። አንደኛዉ ሠላም ማደፍረስ ነዉ። በዝህ ረገድ ሰዉን ለመግደል እና ንብረት ለማዉደም ቅጥረኛን አሰልጥነዉ ከብዙ ገንዘብ ጋር አሰማርቷል። በተለያዩ ቦታዎች በየቀኑ ቦምብ እየተያዘ ነዉ። በየቦታዉ ሰዉ ሲሞት እና ንብረት ሲወድም ስጋት ይሰፍናል። የኢትዮጵያ ህዝብ ሠላም ካጣ የዶር አብይን አስተዳደር ጠልቶ የጅቦችን አገዛዝ ይመኛል። ያኔ ጅብ የሚፈልገዉን ያገኛል።
ሁለተኛዉ ደግሞ የኢኮኖሚ አሻጥር ነዉ። ጅቦች በተደራጀ ሌብነት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በበላይነት ተቆጣጥሯል። ብዙ ሸቀጦች በእነሱ እጅ ነዉ። ይህን አቅም በመጠቀም የገበያን ነፃ ዉድድር ለማወክ አቅዷል። ገባያ ሲዛባ አርተፍሻል እጥረት ይፈጠራል። ይህ ህዝብን ለረሀብ ይዳርጋል። ህዝብ ደግሞ ሲራብ በዶር አብይ አስተዳደር ላይ ይነሳል። በዝህ መሀል ጅብ ወደ ስልጣኑ ይመለሳል። ስሌቱ ይህን ይመስላል።
ስለዝህ ምን እናድርግ? ዋናዉ ጉዳይ ይህ ነዉ። ተጨማሪ ነፃነትን እንጅ ባርነትን አንሻም! ያገኘነዉን ዉጤት ለማስጠበቅ እና ተጨማሪ ስኬት ለማስመዝገብ ደግሞ ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋፅኦ ማድረግ አለብን።
1. እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በያለበት የሀገሩ ደህንነት ሆኖ የጅቦችን እንቅስቃሴ በአንክሮ መከታተል አለበት። አዲስ ነገር ባዬ ጊዜ በመረጃ አስደግፎ ለፀጥታ አካላት ያሳዉቅ። ሰላማችን በእጃችን ላይ ነዉ።
2. የኢኮኖሚ ችግርን በተመለከተ
ሀ. አያንዳንዳችን አሻጥረኞችን እንከታተል። ችግር ከተከሰተ ተጠያቂዉ መንግስት ሳይሆን የቀን ጅብ መሆኑ ከወዲሁ ይታወቅ።
ለ. ሀገር ወዳድ በለሀብቶች የሚፈጠሩ ክፍተቶችን ለመሙላት ከወዲሁ ዝግጅት ያድርጉ።
ሐ. መንግስት ችግሮችን ወደ ዕድል ይቀይር። የኢኮኖሚ አሻጥረኞችን በጥብቅ ተከታትሎ ንብረታቸዉን በመዉረስ ለህዝብ ጥቅም ያዉል። በቦታቸዉ ደግሞ ስራ አጥ ወጣቶችን አሰልጥኖ እና አደራጅቶ ያስገባ። ጫዉ ለራሱ ሲል ይጣፍጣል።
3. የኢትዮጵያ የፀጥታ ሀይል አባላት ከህዝብ ጋር እጅና ጓንት በመሆን ለሀገራቸዉ አንድነት እና ሠላም ዘብ መቆም አለባቸዉ።
ህብረታችን የማይንደዉ ተራራ የለም! የተባበረ ህዝብ ሁሌም አሸናፊ ነዉ!
ሠላም ዋሉ!

► መረጃ ፎረም - JOIN US