tirsdag 27. juni 2017

በቢሊዮን የሚቆጠር ብር የወጣባቸውና 25ሺ ያህል እስረኞችን የሚይዙ አዳዲስ ወህኒ ቤቶች በአራት ክልሎች ተገነቡ

ኢሳት (ሰኔ 20 ፥2009)
በቢሊዮን ብሮች ወጪ 25 ሺህ ያህል እስረኞችን የሚይዙ ወህኒ ቤቶች በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ፣ በዝዋይና በሸዋሮቢት መገንባታቸው ታወቀ። አዲስ ፎርቹን የእንግሊዘኛ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ እንደዘገበው የአዲስ አበባ እስር ቤት 900 ሚሊዮን ብር የወጣበት ሲሆን በአንድ ጊዜ 6 ሺህ እስረኞችን የመያዝ አቅም አለው።
በአዲስ አበባ ከተማ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አባሳሙኤል ወንዝ አቅራቢያ በ5ሺህ ስኩዌር ኪሎሜትር ላይ የተዘረጋው ይህ ወህኒ ቤት ስራው የተጀመረው በሰኔ ወር 2006 መሆኑም ተመልክቷል።
የእስረኞቹ ማቆያ እያንዳንዳቸው ሁለት ፎቅ ያላቸው 5 ብሎኮች ሲሆኑ እያንዳንዱ ብሎክ 1ሺህ 200 እስረኛ እንደሚይዝም ተመልክቷል።
ግንባታው 95 በመቶ ተጠናቋል የተባለውና 6ሺህ እስረኞችን የመያዝ አቅም ያለው ወህኒ ቤት CCTV  ካሜራዎችን ጨምሮ የምስጢር የድምጽና የምስል መቅረጫዎች የተገጠሙበት እንደሆነም ተገልጿል። በሕወሃቱ የጦር ጀኔራል ሜ/ጀኔራል ተክለብርሃን ወልደ አረጋይ የሚመራው ኢንሳ ወይንም የመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ የስራው መሳሪያዎቹን የመትከሉን ሃላፊነት እንደወሰደም መረዳት ተችሏል።
የፌደራሉን መንግስት እስር ቤቶች የመገንባቱ ስራ ከአዲስ አበባ ባሻገር በድሬዳዋ፣ በሸዋሮቢትና በዝዋይ መቀጠሉና መጠናቀቁም ታውቋል።
በሸዋሮቢት 4ሺህ 800 እስረኞችን የሚይዝ ወህኒ ቤት የተገነባ ሲሆን በድሬዳዋም በተመሳሳይም 5ሺህ ያህል እስረኞችን የሚይዝ ወህኒ ቤት መሰራቱም ተመልክቷል።
በዝዋይ የተገነባው ወህኒ ቤት ከአዲስ አበባው ጋር በተመሳሳይ መጠን 6ሺህ ያህል እስረኞችን የሚይዝ መሆኑን ከአዲስ ፎርቹን ዝርዝር ዘገባ መረዳት ተችሏል።

mandag 26. juni 2017

Hundreds of thousands of Ethiopians face deportation in Saudi Arabia

ESAT News (June 26, 2017)
Hundreds of thousands of Ethiopians in Saudi Arabia face monetary penalty and imprisonment as the Kingdom’s amnesty for undocumented workers expired on June 25.
Ethiopian government spokesperson, Negere Lencho told local media that of the 85,000 who took travel documents, only about 35,000 have returned home. It is estimated that about 700,000 Ethiopians live in the Kingdom and a great majority of them are undocumented.
The government of Saudi Arabia in March decreed a 90 day amnesty for undocumented workers to leave the Kingdom and legally return if they wish to.
The hundreds of Ethiopians who haven’t obtained their travel documents now face penalty and imprisonment which will be followed by deportation. The Ethiopians in the Kingdom have been accusing their government of not facilitating their return. They said while citizens of other countries have been provided by their government free transportations, ticket prices from the Ethiopian airlines have become unaffordable for them.
The spokesperson for the Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia, Meles Alem said his Ministry has requested Saudi Arabia for an extension of the amnesty;but it is not yet known if Kingdom responds positively.
Maj Gen Sulaiman Al-Yahya, director general of passports in Saudi Arabia, said last week more than 400,000 foreigners completed final exit procedures by taking advantage of the three-month amnesty, according to Saudi Gazette.
He warned that there won’t be any leniency towards those violators who failed to benefit from the amnesty.

søndag 25. juni 2017

ናታችን እና የቁርጠኝነታችን ዓርማ ነው!!

June 24, 2017 
አንዳርጋቸው ጽጌ
የንቅናቄያችን መስራችና ዋና ጸሀፊ የነበረው ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ በዘረኛው የህወአት አገዛዝ ከየመን አየር ማረፊያ ታግቶ እስር ቤት ከተወረወረ እነሆ ጁን 23 2017 ዓም 3 አመት ሞላው።
ህወአት አንዳርጋቸውን ባገተበት ወቅት የንቅናቄያችን እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ይሽመደመዳል የሚል ተስፋና እምነት ነበረው። ይህንን እምነቱን ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ በሚፈጸምበት ሰቆቃ ውስጥ ሆኖ እንዲያረጋግጥለትና ነጻነት ናፋቂ የሆነው ህዝባችን ተስፋ እንዲቆርጥ ብዙ ጥሯል፣ ደክሟል።
የኢትዮጵያ ህዝብ በሚከፍለው ግብር የሚተዳደረው የአገራችን ዋናው ቴለቪዥን ጣቢያና ህወሃት ህዝባችንን በፕሮፖጋንዳ ለማደንዘዝ ያቋቋማቸው ሌሎች ሚዲያዎ በሙሉ በመረባረብ ከጓዳችን መታገት ጋር ተያይዞ ግንቦት 7 አከርካሪውን ተመቶአል፤ ሌሎች የንቅናቄው አመራሮች የአውሮጳና የአሜሪካ የምቾት ኑሮዋቸውን ትተው ወደ በረሃ የመሄዳቸው ጉዳይ የማይታሰብ ነው የሚል ከንቱ ትንበያ ከማራገብ አልፈው የህዝባችንን ቅስም ለመስበር ያመቸናል የሚሉትን የፈጠራ ድራማዎችን በማቀነባበርና በማሰራጨት ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን ብቻ ሳይሆን ግምቱ የማይታወቅ የአገራችንን ሃብትም አባክነዋል።
ህወሃት ከህዝብ በተዘረፈ ገንዘብና በጠመንጃ ሃይል በተያዘ ሥልጣን ልቡ ያበጠ እብሪተኛ ድርጅት መሆኑን በገሃድ ያስመሰከረው ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌን ለማገት ከተጓዘው ርቀት እና ከወሰደው የድፍረት እርምጃ በተጨማሪ ለነጻነት የሚደረገው ትግል አብቅቶለታል ብሎ ለመደምደም ያሳየው ጥድፊያ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት ትግል ፤ ለፍትህ ለእኩል ነትና ለአገር ባለቤትነት የሚደረግ ትግል መሆኑ መረዳት ያልቻለው የህወሃት አገዛዝ ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ ከአፍላ የወጣትነት ዕድሜው ጀምሮ የቆመለትና ዋጋ እየከፈለለት ያለው ይህ ክቡር አላማ ከግለሰብ ተክለ ሰውነት በላይ ግዙፍ እንደሆነ አንዳርጋቸውና የትግል ጓዶቹ ጠንቅቀን እናውቃለን።
ወያኔ አገር ውስጥ ያሉትን ተቃዋሚዎች እግር በእግር እየተከተለ ለማዳከም በየቀኑ የሚወስደው የእስር፤ የእንግልትና የግዲያ እርምጃ አልበቃ ብሎት ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌን ከባህር ማዶ አግቶ ለመውሰድ ለየመን ጸጥታ ሃይል በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከፍሎአል። በዚህ የወያኒ የእብሪት እርምጃ የተበሳጨው የኢትዮጵያ ህዝብ ዘር፤ ቋንቋና ሃይማኖት ልዩነት ሳያከፋፍለው ‘”እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ” በሚል ቁጣ ተነስቶ በአምባገነንነትና በዘረኝነት ላይ የሚደረገውን ትግል ወደ ሌላ ምዕራፍ እንዲሸጋገር አድርጎታል። ከዚህም በተጨማሪ ህወሃት ከአንዳርጋቸው መታገት በኋላ በአመራር እጦት ይበተናል ያለው የነጻነት ትግል ከኢትዮጵያ አርበኞች ግንባር ጋር በተደረገው ውህደትና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በጋራ ለመታገል በተፈጠረው ጥምረት መክሸፉን አስመስክሯል።
ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ በታገተ ሰሞን የንቅናቄያችን አመራር ወደ ምድር ወርዶ ትግሉን ለመምራትና ለመታገል ያስተላለፈውና እየተገበረው ያለው ውሳኔ በጠላት ካምፕ ከፍተኛ መደናገጥን ሲፈጥር በወገን ካምፕ በኩል ከፍተኛ ተስፋንና አለኝታነትን የጫረ ሆኖአል።
የንቅናቄያችን አርበኞች ግንቦት 7 አባላት እና ደጋፊዎች በየምንሰበሰብባቸው የስብሰባ አዳራሾችና በየምንሰማራባቸው የትግል መስኮች እየዘመርነው ያለው የ”ላንቺው ነው አገሬ” ግጥም ደራሲ የሆነው ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ የምንታገልለትን አላማ በአጭሩ እንዲህ ሲል በስንኞቹ አስቀምጦአል።
በባርነት ሸክም ጀርባሽ የጎበጠው፣
በባለጌ መዳፍ ክብርሽ የጎደፈው፣
የስቃይሽ ስቃይ ሰማይ የነደለው፣
ዓይንሽ እስኪጠፋ ደም ለምታነቢው፣
ላንቺ ነው ሀገሬ ህይወት የገበርነው፣
ላንቺው ነው ሀገሬ እኛ የምንሞተው።
ለናዱት አንድነት ላረከሱት ሀገር፣
ለቀሙን ነጻነት ለጫኑብን ቀንበር፣
መልሱ ሆኖ መጥቷል ደረትን ለአረር፣ እያለ ይቀጥላል።
ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ ይህንን ግጥም በደረሰበት ወቅት በእአምሮ ውስጥ ይመላለስ የነበረው አገራችን የገባችበት አዘቅትና የህዝቦቿ ጉስቁልና እንደሆነ መገንዘብ ከባድ አይሆንም። ይህንን ለመለወጥ ደግሞ ትግሉ የሚጠይቀው ቁርጠኝነትና የመንፈስ ጽናት ደረጃ እስከምን እንደሆነ በግልጽ አስቀምጦአል።
መላው የንቅናቄያችን አባላትና ደጋፊዎች መሪያችን አንዳርጋቸው ጽጌ በጠላት እጅ የወደቀበትን ሶስተኛ አመት ስናስታውስ እርሱና ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላቶቻችን እስከዛሬ የከፈሉትንና በመክፈል ላይ የሚገኙትን መስዋዕትነት እያሰብን ይህ ሁሉ ዋጋ የተከፈለለትን የነጻነት ትግል ከዳር ለማድረስ ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ በመግለጽ ነው ።
ዛሬ በየእስር ቤት ውስጥ ሆነው በንቅናቄያችን አርበኞች ግንቦት 7 ሥም የተለያየ መከራና ስቃይ በመቀበል ላይ ያሉትም ሆኑ በትግሉ ላይ እያሉ ውድ ህይወታቸውን ለዚህ ክቡር ዓላማ የገበሩ ወገኖቻችን የሚካሱት እነርሱ ዋጋ የከፈሉለትን አላማ ከግብ ለማድረስ ባለን ጽናትና ቁርጠኝነት ብቻ ነው።
የጀመርነው ትግል ምንም አይነት ዋጋ ቢያስከፍለን የኋላ ኋላ በአሸናፊነት እንደሚደመደም ምንም አይነት ጥርጣሬ የለንም። መታሠር፣ መገረፍና መገደል የነጻነት ትግል ማደናቀፍ የሚችል ቢሆን ኖሮ የህወሃት የመንፈስ አባት የሆነው ፋሽስት ጣሊያን እስከዛሬዋ ደቂቃ ድረስ በባርነት ሲገዛን ይኖር ነበር።
ውድ ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ እና በተለያየ የወያኔ ማጎሪያ ቤቶች ውስጥ ፍዳችሁን እያያችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን ሆይ! የታሠራችሁበት የብረት ሰንሰለትና የታገታችሁበት የእስር ቤት በሮች የሚበረገዱበት ቀን ሩቅ እንደማይሆን እኛ የትግል ጓዶቻችሁ እናረጋግጣለን። በአረአያነት ያስተማራችሁን ጽናታችሁና ቆራጥነታችሁ በደማችን ውስጥ ነፍስ እንደዘራ አትጠራጠሩ።
ዘለአለማዊ ክብር ለነጻነት ስሉ መስዋዕትነት ለከፈሉ ጀግኖቻችን ሁሉ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

fredag 23. juni 2017

Ethiopia crises force millions out of school

From ADANE BIKILA in Addis Ababa, Ethiopia,
ADDIS ABABA, (CAJ News) – MILLIONS of children are out of school in Ethiopia as the East African country endures successive natural disasters and conflict.According to the Education Management Information System (EMIS) of ministry of education, the number of children and teachers affected by the crises increased from 2,1 million in December 2015 to 4 million in June 2016.
However, the number has decreased to about 3 million between November and December 2016 but is still cause for concern.The Nations Children’s Fund (Unicef) said shortage of water and school feeding had been identified as a major contributor to student absenteeism and dropouts.
Assessment data reveal that about 76 percent of primary schools in nine regions have no water available on school premises and 47 percent of schools are without latrines.“As a result, children’s school attendance is erratic and in some cases children dropout of school entirely due to families migrating in search of water,” said Unicef spokesperson.It is estimated that about 2 million school-age children in hotspots require school feeding in 2016/17 academic year.In many affected areas teachers reported a lack of student attentiveness in the classroom and low attendance rate due to limited provision of school feeding.
The loss of assets and livelihoods due to the drought has also compromised the capacity and purchasing power of parents and care givers to send their children to school.Parents are unable to cover the costs of school uniforms and learning supplies.It is also estimated that about 2 million school-age children need school implements.The UN’s International Office of Migration reported that 147 366 school age children were displaced due to the impact of the current drought, the worst in 30 years, flooding and communal conflicts.
– CAJ News

torsdag 22. juni 2017

የአንበጣው መንጋ የወረራቸው አካባቢዎች የመንግሥት እገዛ ተነፍጓቸዋል

በምዕራብ ጎጃምና አዊ ዞኖች የገበሬውን ሀብት ንብረት የሚያወድም አደገኛ አንበጣ ተከስቷል፡፡ አንዱ የአንበጣ መንጋ በቀን 16 ኪሎ ሜትሮችን መጓዝ የሚችል ሲሆን ባሕር ዛፍን ጨምሮ ማንኛውንም ዓይነት ሰብልና እጽዋት መድምዶ በመብላት ያወድማል፡፡ በምዕራብ ጎጃምና በአዊ ዞኖች ከአራት ወረዳዎችና ከ50 በላይ ቀበሌዎች በአንበጣው መንጋ ተወረዋል፡፡ አንበጣው የሚመርጠው የለም፤ ገበሬዎች ‹‹ሁሉን በይ አንበጣ›› ይሉታል፡፡ የግብርናና የልማት ባለሙያዎች ለክልሉ መንግሥት ግብርና ቢሮ አንበጣው መጥፋት የሚችልበትን መድኃኒት ወይም ማንኛውም ዓይነት እገዛ ቢጠይቁም በአገር ውስጥ ለዚህ ዓይነት አንበጣ መከላከያ የሚሆን መድኃኒት የለም የሚል መልስ እንደተሰጠ ሰምተናል፡፡ አስቸኳይ ርብርብ ተደርጎ መከላከል ካልተቻለ በስተቀር አጠቃላይ የምዕራብ ጎጃምንና የአዊ አካባቢዎች ያለውን ሰብልና እጽዋት አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሊያወድም ይችላል ተብሏል፡፡ እስካሁን ድረስ ባለው ከሃምሳ በላይ ቀበሌዎች በበልግ ዝናብ የበቀለ ሰብልና በአካባቢው ያለውን እጽዋት ሁሉ እንዳወደመ ለማወቅ ተችሏል፡፡

torsdag 15. juni 2017

ለሶስተኛ ጊዜ ተቀጥሮ የነበረው የባሕር ዳር የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የዋስትና መብት ጥያቄ ዳግም ውድቅ ተደረገ

ለዛሬ ሰኔ 7/2009 ዓ.ም ፡፡
(በሰማያዊ ብሔራዊ ሸንጎ የህዝብ ግንኙነት ንዑስ ኮሚቴ)
****************************************
«በከፍተኛ የአገር ሃብትና የሰው ህይወት ውድመት » ተጠርጥራችኃል በሚል አስር ወራቶች በእስር የቆዩት የሰማያዊ ፓርቲ የባህር ዳር አመራሮች ዳግም ያነሱት የዋስትና መብት ተነፍገው በባህር ዳር ማረሚየ ቤት እንዲቆዩ ሲል ፍርድ ቤቱ ዛሬ ከሰዓት በዋለው ችሎት ወሰነባቸው። በማረሚያ ቤት ሁናችሁ ጉዳያችሁን ተከታተሉ የተባሉት ታሳሪዎቹ “የትኛውን ጉዳይ” ብለው ቢጠይቁ ዳኛው መልስ እንደሌለው የተናገረው የታሳሪዎቹ ጠበቃ አዲሱ ጌታነህ
« የአንድ ምርመራ መዝገብ ማለቅ ያለበት በ15 ቀን ውስጥ ነው። ይህ ቀን በቂ አይደለም ከተባለ በፍርድ ቤት ተቀርቦ ተጨማሪ ቀናት ይጠየቃል እንጂ ምንም ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ባልተጠየቀበት ሁኔታ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩ ባለታወቀበት ምክንያት በማረሚያ ቤት ሁናችሁ ጉዳያችሁን ተከተተሉ ማለቱ አገሪቱ ያለችበትን ስር የሰደደ ህገ ወጥ የሆነና የህግ መሰረት የሌለው በተጨማሪም በአገሪቷ ላይ ፍትህ አልባነትና ምን ያህል እንደነገሰ አመላካች ድርጊት ነው ብሏል።» ፓርቲውን ለማዳከም ሲባል ብቻ ክስ ሳይመሰረትባቸው ከአስር ወራቶች በላይ ታስረው መራራ መስዋትነት ካለ ምንም ጥፋታቸው እየከፈሉ ያሉት አመራሮች አቶ ማሩ ዳኘው፣ አቶ መልካሙ ታደለ፣ አቶ ሲሳይ ታከለ፣ አቶ እጅጉ አስማረ እና አቶ ወርቁ ጥላሁን ናቸው።

onsdag 14. juni 2017

Ethiopia’s heavy dependence on foreign aid increasing

ESAT News (June 14, 2017)
Ethiopia says it expects a third of its budget to be covered with aid from donor countries and foreign loans.
Presenting the country’s 2017/2018 budget to the parliament, the minister of finance and economic cooperation announced that of the total 321 billion birr (14 billion dollars) allocated for the budget year, about 5 billion dollars is expected to be covered from donors.
The minister, Abraham Tekeste, said the country’s defence budget has been increased from 478.3 million to 521.8 million dollars. On the contrary, the money allocated for sustainable development projects has been reduced from 522 million to 304.3 billion dollars.
Analysts say the increase in defence expenditure and the decrease in the budget for economic projects show the regime has given priorities in averting the security threat it faced from its neighbours and armed political forces in and outside the country.
Analysts also said the regime’s plan to cover one third of the economy from aid and loan contradicts the economic miracle the country is said to have achieved, as propagated by the oligarchy and its foreign allies.

mandag 12. juni 2017

አርበኞች ግንቦት 7 ለመጀመርያ ጊዜ አዲስ አበባ ላይ ጥቃት መፈፀሙን ገለጠ

በሰሜን ጎንደር አንድ የሱዳን ተሳቢ የፈሳሽ መጫኛ መኪና ከሱዳን ተነስቶ በመተማ መንገድ በማለፍ ጣራገዳም ተራራን ጨርሶ አዲስ ዘመን ከተማ ለመግባት 2 ኪሎ ሜትሮች ሲቀረው የንቅናቄው ታጋዮች በወሰዱት ጥቃት የመኪናው ሹፌር እና የመኪናው ጎማ እንደተመታ ተሳቢውንና መኪናው ለየብቻ መውደቃቸውን በፎቶ ግራፍ አስደግፎ የላከው መረጃ ያመለክታል። የመኪናው አሽከርካሪ ባህርዳር ለህክምና ቢወሰድም ህይወቱ አልፏል። መኪናው ነዳጅ አለመጫኑ ታውቋል።
በተመሳሳይ ዜና የንቅናቄው ሰኔ 4 ቀን 2009 ዓ/ም፣ ከቀኑ 5:00 ሲሆን በጭልጋ ወረዳ ሹታራ ቀበሌ ወደ ሚገኘው የኮማንድ ፖስት ጽ/ ቤት ሰርገው በመግባት የአካባቢውን ህብረተሰብ አፍነው በማምጣት የሚያሰቃዩበት አስር ቤት እና እንደ ጽ/ቤት የሚገለገሉበት ክፍል ሙሉ በሙሉ ማውደማቸውን ድርጅቱ ገልጿል።በጥበቃ ላይ የነበሩ ፖሊሶች ራሳቸውን ለማዳን መሸሻቸውን ታጋዮችም በሰላም ወደ ቦታቸው መመለሳቸውን ድርጅቱ አስታውቋል።
በሌላ በኩል ባለፈው ባለፈው ቅዳሜ፣ ሰኔ 3 ቀን 2009 ዓ.ም አንድ የአርበኞች ግንቦት 7 የአዲስ አበባ ህዋስ አዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ከቀድሞ ናዝሬት አውቶቡስ ተራ አጠገብ የሚገኘውን የህወሓትን የድብቅ ማሰቃያ ቦታ እና የመሣሪያ ማከማቻ ማውደሙን ድርጅቱ ገልጿል። ቦታው ቀደም ባሉ ዓመታት የጉምሩክ መጋዘን ሆኖ ያገለግል እንደነበር የገለጸው ድርጅቱ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን ቦታው ለፌደራል ፓሊስ የመሣሪያ ግምጃ ቤትነትና በስውር ማሰቃያነት እያገለገለ ነበር ብሎአል።
“በርካታ ወገኖቻችን ዓይኖቻቸው እየታሰሩ ወደዚህ ቦታ እየተወሰዱ ስቃይ (ቶርቸር) እንዲደርስባቸው በመደረጉ ለዘላቂ የአካልና የስነልቦና ጉዳት ተዳርገዋል” ፣ ያለው ንቅናቄው፣ “በዚህ ግቢ ውስጥ በርካታ ወንድና ሴት እስረኞች እጅግ አሰቃቂና ኢሰብዓዊ በደል ተፈጽሞባቸዋል። በዚህ ግቢ ውስጥ በደሰረባቸው ስቃይ ምክንያት ዘር ማፍራት እንዳይችሉ የተደረጉ ወገኖቻችን በርካቶች ናቸው። ህይወታቸው ያለፈው ዜጎች ቁጥርም በርካታ ነው። በዚህ ፀረ ትውልድ እና ፀረ ኢትዮጵያ ተቋም ላይ” የአርበኞች ግንቦት 7 የአዲስ አበባ ህዋስ እርምጃ ወስዷል ብሎአል።
በተወሰደው ጥንቃቄ የተሞላበትና የተጠና እርምጃ ሳቢያ በግቢው ውስጥ የነበሩ መጋዘኖች ከነመሣሪያዎቻቸው በእሳት እንዲጋዩ መደረጉን የሚገልጸው ድርጅቱ፣ የአዲስ አበባ ነዋሪ የተወሰደውን እርምጃ በዓይኖቹ እንዲያይና በህወሓት አምባገነን አገዛዝ የሚደርስበት ስቃይ ቁጭት እንዲወጣ እድል የፈጠረ እርምጃ ነበር ብሎአል። በተወሰደው እርምጃም የፌደራል ፓሊስ አባላት የህቡዕ እርዳታ ማድረጋቸውን ገልጿል።
ለወደፊቱም ተመሳሳይ እርጃዎች ሊወሰዱ እንደሚችሉ የአርበኞች ግንቦት 7 የአገር ውስጥ ህቡዕ አመራር ገልጾ፣ እያንዳንዱ አገሩንና ነፃነቱን የሚወድ ዜጋ በየተሰማረበት መስክ ሥርዓቱን የሚያዳክሙ የሕዝባዊ እምቢተኝነትና የሕዝባዊ አሻጥር እርምጃዎችን ተግባራዊ እንዲያደርግ አሳስቧል።
በጥቃቱ ዙሪያ ከገዢው ፓርቲ በኩል የተሰጠ መልስ የለም።
ኢሳት ዜና

mandag 5. juni 2017

Ethiopia: Regime forces dealt with serious blow, says Prof. Berhanu Nega

ESAT News (June 5, 2017)
A leader of an opposition group says Ethiopian regime forces have been dealt with a serious blow in a two-day fight in Gondar.
Speaking to supporters at a public meeting in Los Angeles on Sunday, Prof. Berhanu Nega, Chairman of the Patriotic Ginbot 7, a group fighting the Ethiopian regime, said it was one of the serious blows to the regime since the start of the armed struggle. He said the regime deployed thousands of its forces to crush freedom fighters led by his group, but instead sustained a major defeat in localities called Ajere and Janora in North Gondar as well as well as in Kemkem and Belesa in the south.
The PG7 leader described the recent fight as heavy with deadly consequences to regime forces.
In a desperate retaliation, regime security forces have rounded up over 200 civilian residents of the city of Gondar while deploying thousands of more troops in the area, according to Nega.
He said regime authorities have resorted to false claims that the attack by Patriotic Ginbot 7 forces was reinforced by Eritrean forces.
Prof. Berhanu Nega said no matter the size of its troops, the regime can not and will not stop the fight by the people of Ethiopia to reclaim their freedom.
Sources meanwhile said the regime has sent troops loaded in 20 trucks to the area following the defeat on Thursday. The sources said regime forces have used heavy machinery and even war planes in fight with the guerrilla forces.

torsdag 1. juni 2017

የአርበኞች ግንቦት 7 የህዝብ ግኑኝነት የነበረው ታጋይ ዘመነ ካሴ ከኤርትራ ለህክምና ወደ አውሮፓ መግባቱ ታውቋል

Ethiopian Patriot Zemene Kassse
አርበኛ ዘመነ ካሴ ለህክምና ወደ አውሮፓ እንዲጓዝ ትልቁን ድጋፍ ያደረገለት ድርጅቱ አርበኞች ግንቦት 7 መሆኑን ከስፍራው ያገኘነው ማስረጃ ያመላክታል።
ከጥቂት ግዚያት በፊት ባጋጠመው ህመም፣ ከትግሉ ላልተወሰነ ግዜ ርቆ የተቀመጠው ዘመነ፣ የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል። ትግል መስዋዕትነት መክፈል መሆኑን ለማወቅ የተሳናቸው ግለሰቦች፣ ዘመነ አንድ ግዜ በኤርትራ እስር ቤት ይገኛል በሌላ ግዜ አርበኛች ግንቦት 7 አስገድሎታል እያሉ የተለያዩ የሀሰት አሉባልታዎችን ሲያሰራጩ መቆየታቸው የቅርብ ግዜ ትዝታችን ነው።
እነዚህ የኪቦርድ ታጋዮች፣ ህይወቱን ለመስጠት በርሃ የገባ ታጋይን ካላሳያችሁን እያሉ ያዙን ልቀቁን ሲሉ መስማት እንጭጭነታቸውን ወይም አለማወቃቸውን በአደባባይ ከማስመስከር ውጭ የትም እንደማይደርሱ መገንዘብ እንኳ የተሳናቸው ናቸው። የዘመነ ፋይል እዚህ ላይ ሲዘጋ ነገ ደግሞ በረሃ ያሉትን ሌሎች ጓዶቻችንን ምክንያት እየፈጠሩ አዲስ የመጨቃጨቂያ አጀንዳ እንደሚከፍቱ ምንም ጥርጥር የለም። በዘመነ ላይ በተወራው ብዙ ማለት ይችላል። ስለዚህ አሉባልታዎችን ትተን የሁላችንም ጠላት የሆነውን ወያኔ አምርረን መታገል አለብን። አሁንም ቢሆን ዘመነ ለህክምና የወጣው በአርበኞች ግንቦት 7 ፍቃድና ድጋፍ እንጅ በኪቦርድ ጩኸት እንዳልሆነ ሊያውቁት ይገባል። ዘመነ ተገድሏል፣ ታስሯል እያሉ ሲያደነቁሩን የነበሩ አሉባልተኞች አውሮፖ መግባቱን ሲሰሙ ምን አርዕስት ይከፍቱ ይሆን?
ከዲሲ ግብረ ሃይል ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ