torsdag 31. oktober 2013

የጉዲፈቻ ልጃቸውን የገደሉ ተፈረደባቸው

ኣንዲት የጉዲፈቻ ልጃቸውን ኣሰቃይተው ለሞት ያበቁ ባልና ሚስት አሜሪካውያን ከ28 እስከ37 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተፈረደባቸው።
Bild I: Adoptiveltern in USA Höchststrafen für Hunger und Unterkühlung Tod von Teenager-Mädchen aus Äthiopien erhalten 2910 2013
Titel: Hana Williams - Larry Williams und Carri von Sedro-Woolley, Washington wurden für schuldig befunden, Vernachlässigung, Missbrauch und schließlich Tötung der 13-jährigen Hana Williams aus Äthiopien.
Autor/Copyright: Azeb Tadesse Hahn DW Bonn - 2013
Schlagworte: Hana Williams´s Grab in Washington State - Seattle
የ13 ዓመትዋ ሐና ዊሊያምስ ህይወቷን ያጣችዉ በጎርጎሪዮሳዊዉ የዘመን ቀመር ግንቦት 12 ቀን 2011ሲሆን ከትናንንት በስተያ ማክሰኞ ዕለት ያስቻለው የሲኣትል ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ ሚስት ወ/ሮ ካሪ ዊሊያምስ 37 ዓመት እና ባል ላሪ ዊሊያምስ ደግሞ 28 ዓመት እንዲታሰሩ ፈርዶባቸዋል።
ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ኣንድ ሌላ እትዮጵያዊ የጉዲፈቻ ልጅን ጨምሮ ስድስት አብራካቸዉ የተገኙ ልጆችም ኣሏቸው።
በ ዩኤስ አሜሪካ ከሴኣትል በስተ ሰሜን 60 ማይልስ ወይንም 100 ኪ ሜ ላይ በምትገኘው መለስተኛ ከተማ ሲድሮ ዊሊ ነዋሪ የሆኑት ካሪ ዊሊያምስ እና ባለቤትዋ ላሪ ዊሊያምስ የራሳቸው 6 የአብራክ ልጆች እያላቸው ከእነዚህ በተጨማሪ ያኔ ሐና ዓለሙ ትባል የነበረችውን ሙዋች ሐና ዊሊያምስን እና የጉድፈቻ ወንድምዋን ዒማኑዔል ዊሊያምስን ከኢትዮጵያ በጉድፈቻ ያመጡኣቸው እ ኣ ኣ በ2008 ዓ,ም ሲሆን ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉት የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የትምህርት ክፍል ኣስተባባሪ ወ/ሮ መታሰቢያ ሙሉጌታ እንደሚሉት ህጻናቱ ከጉዲፈቻ ቤተሰቦቻቸው ጋር በሰላም የኖሩት የመጀመሪያውን ዓመት ብቻ ነው።
ሀና ዊሊያምስ ሞታ የተገኘችው በ3ኛ ዓመትዋ መሆኑ ነው ኣሁንም እንደ እ አ ኣ ግንቦት 12 ቀን 2012ዓ ም ሲሆን ኣሙዋሙዋትዋም ወ/ሮ መታሰቢያ እንደሚሉት የምግብ እጥረትን ጨምሮ ተደብድባ መሆኑን ኃኪሞች መስክረዋል።
Bild I: Adoptiveltern in USA Höchststrafen für Hunger und Unterkühlung Tod von Teenager-Mädchen aus Äthiopien erhalten 2910 2013
Titel: Hana Williams - Larry Williams und Carri von Sedro-Woolley, Washington wurden für schuldig befunden, Vernachlässigung, Missbrauch und schließlich Tötung der 13-jährigen Hana Williams aus Äthiopien.
Autor/Copyright: Azeb Tadesse Hahn DW Bonn - 2013
Schlagworte: Hana Williams´s Grab in Washington State - Seattle
በመካከሉ ጉዳዩ እንደ መቀዛቀዝ ማለቱ ባይቀርም የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አባላት ባለመታከት ባደረጉት ክትትል የችሎቱ ሂደት እንደገና ተፋጥኖ ባለፈው ማክሰኖ በዋለው ችሎት ኣንደኛ ተከሳሽ ወ/ሮ ካሪ ዊሊያምስ በ37 ዓመት ጽኑ እስራት እንድትቀጣ ተፈርዶባታል። 37 ዓመት በአሜሪካ የመጨረሻው ረጅሙ ቅጣት ሲሆን ዳኛ ሱዛን ኮክ እንደሚሉት እንዲያውም ወንጀለኛዋ እድሜዋ ከፈቀደ ከዚያም በላይ በወህኒ ቤት ልትቆይ ትችላለች።
2ኛው ተከሳሽ እና የቦይንግ ኣውሮፕላን ፋብሪካ ሰራተኛ የሆነው ባል ላሪ ዊሊያምስ ደግሞ የ28 ዓመት ጽኑ እስራት ተፈርዶበታል። የሁለቱም ክስ ከሀና ዊሊያምስ ግድያ በተጨማሪም የወንድሙዋ ዒማኑዔል ዊሊያምስ በደል እና ድብደባንም ያካትታል።
ሁለቱ ወንጀለኛ ጥንዶች ከችሎት በቀጥታ ወደ ወህኒ ከተላኩ በኃላ ዒማኑዔል ዊሊያምስን ጨምሮ ስድስቱ የአብራክ ልጆችም ወዲያውኑ ለጉድፈቻ ተቋም መሰጠታቸውም ታውቀዋል።

የአንድነት ፓርቲ አቤቱታ


አንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ በአጭሩ አንድነት፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት አባሎቼ ላይ ግድያና ወከባ ተፈጽሟል ማለቱን አዣንስ ፍራንስ ፕረስ ከአዲስ አበባ ዘገበ። የፓርቲዉ ሊቀመንበር ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳን የጠቀሰዉ ዘገባ በደቡብ ኢትዮጵያ የፓርቲዉ አባላት ላይ ግድያ መፈጸሙን ከ150 በላይም ወከባ፤ ያል ክስ እስራት እንደደረሰባቸዉ መግለጻቸዉን አመልክቷል። የኢትዮጵያ መንግስት የተባለዉን ዘገባ አለመመልከቱን መግለፁንም ዘገባዉ ጨምሮ ገልጿል። 

ደቡብ ወሎ ወረባቦ በእሳት እየወደመች ነው



ደቡብ ወሎ ወረባቦ በመንግስት ቅጥረኛ ተላላኪወች እና ከወገናቸው ጋር በቆሙ ( ከስርዓቱ ባፈነገጡ ) ምልሻወች በተነሳ ግጭት እንዱ የመንግስት ተወካይ በሌላኛው መኖሪያ ቤት ላይ በለኮሰው እሳት ቃጠሎ ተነስቶ ብዙ ጉዳት እየደረሰ ነው ;

ዛሬ ከቀኑ 7 ሳሃት ጀምሮ በወረባቦ ከተማ በቀበሌ ፩፪ ልዩ ስሙ ማሊ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተነሳው እሳት ብዙ መኖሪያ ቤቶቺን ,የቀንድ እና የጋማ ከብቶችን የፈጀ ሲሆን እስካሁን ድረስ ከ ፪፭ በላይ መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል , እሳቱን ለማጥፋት ብቂ ኃይል ስላልነበረ እስካሁን በከፍተኛ ፍጥነት ወደሌላ አካባቢ በመስፋፋት ላይ ይገኛል ::

onsdag 30. oktober 2013

በምሥራቅ ጎጃም የሚገኘው የዳገት እየሱስ ቤተክርስቲያን ባልታወቁ ሰዎች የቃጠሎ አደጋ ደርሶበታል



በምሥራቅ ጎጃም የሚገኘው የዳገት እየሱስ ቤተክርስቲያን ባልታወቁ ሰዎች የቃጠሎ አደጋ ደርሶበታል፥ ባለፉት ጥቂት ወራቶች ውስጥ በዚሁ መምሥራቅ ጎጃም ሃገረ ስብከት ውስጥ በጠቅላላው ወደ 4 የሚጠጉ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት የቃጠሎ አደጋ እንደደረሰባቸው ከሥፍራው የደረሰን ሪፖርት ያሳያል።
በሃገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ቤተክርስቲያናት፣ አድባራት፣ ገዳማት እንዲሁም የአብነት ትምህርት ቤቶች ባለፉት 20 ዓመታት ሲቃጠሉ፣ ሲወድሙ ተመልክተናል ነገር ግን ቤተክህነቱ ምንም ሊያደርግ አልቻለም ወይንም የእምነቱ ተከታዮች ምንም ማድረግ አልቻሉም ወይንም አይመለከተንም ብለው ተቀምጠዋል። በጣም በእጅጉ የሚያስፈራው በቀጣይነት ክርስቲያኖች በየቦታቸው እየታደኒ አደጋ እንዳይደርስባቸው ስጋት አለን። እግዚአብሔር ይሁነን
የወያኔውች ስራ ነው ይሄን ቦታ ሊያስለቅቋቸው መሆን አለበት እንጂ እንዴት ይሄ ሁሉ ቤተክርስቲያን አንድ ዓመት ያውም አራት ወር ባልሞላግዜ ውስጥ ይቃጠላል?አገር አስተዳድራለሁ የሚለው መንግስት ተብየው እንዴት ዝም አለ?እጁ ቢኖርበትም አይደል?
ቤተክርስቲያንንና ገዳማትን ከጥቃት ለመከላከልና የፈረሱትንና የተቃጠሉትን ለመስራት የበኩሉዎን አስተዋፆ ያደርጉዘንድ ይለመናሉ::

ኢትዮጵያ- የፖሊስ መንግስት ያንሰራፋባት ሀገር (ከፕ/ር አለማየሁ ገብረ ማርያም)

የኢትዮምህዳር ጋዜጠኞች አደጋና ውሳኔ

አደጋው ከደረሰባቸው ጋዜጠኛ አንዱ ጌታቸው ወርቁ እንዳስታወቀዉ ለአደጋ የተጋለጡት የተሳፈሩበት ባጃጅ በሞተር ብስኪሌት በመገጨቱ ነዉ።የሃዋሳ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም መከሰስ ያለበትም ዋና አዘጋጁ ነው ሲሉ ጋዜጠኞቹ ያቀረቡትን ጥያቄ ዛሬ ከሰዓት ውድቅ አድርጓል።
ሶስት የኢትዮ ምህዳር ጋዜጠኞች ዛሬ በሃዋሳ ከተማ በደረሰባቸው የግጭት አደጋ መጎዳታቸዉን አስታወቁ ። ጋዜጠኖቹ አደጋው የደረሰባቸው ስለ ሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ባወጡት ዘገባ ለቀረበባቸው ክስ የሲዳማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰጣቸው ቀጠሮ መሰረት ሃዋሳ በተገኙበት ወቅት ነበር።አደጋው ከደረሰባቸው ጋዜጠኛ አንዱ ጌታቸው ወርቁ እንዳስታወቀዉ ለአደጋ የተጋለጡት የተሳፈሩበት ባጃጅ በሞተር ብስኪሌት በመገጨቱ ነዉ።የሃዋሳ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም መከሰስ ያለበትም ዋና አዘጋጁ ነው ሲሉ ጋዜጠኞቹ ያቀረቡትን ጥያቄ ዛሬ ከሰዓት ውድቅ ማድረጉን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ከአዲስ አበባ ዘግቧል ።

Debre Markos University says ESAT, other forces behind students’ protest

The administration of DebreMarkosUniversity has admitted that students of the University have been on a hunger strike. The protest began after students refused to accept thegovernment’s new “regulation on dressing, dinning, and worship”.

The students complain that they have been forced to stop practicing their faith and cut their religious strings from their necks.

In his discussion with the officials of the region, Deputy President of the University, Dr. Negusie Miteku, said that although there have been attempts to apply the regulation in the previous academic year; it has not been effected as the students have refused to accept it. The students also complain that the daily food allowance approved by the Council of Ministers is 12 birr, ‘which does not even buy a loaf of bread and tea in Debre Markos town.’

The Deputy President confirms that the students’ question has been correct and the students’ food budget is meagre. He said they have gone beyond the government’s allowance to subsidise the budget. Negusie admitted that there has also been a decrease in the gram of bread from 80 to 45 per the evaluations and criticisms of the government.  However, when students got the loaf of bread weighed they were found to be weighing between 25 to 30 grams.

Information found within the Ministry of Health indicates that at least 32 students have been sick due to lack of food during the start of the academic year.

The Deputy President argues “looking at the timing of ESAT’s reporting of the protests, it is possible to tell that the students’ protest is not just in relation to the new regulations but that ESAT and other forces are behind the protest”.

The windows of six buildings have been fully damaged and three ambulances have been destroyed due to the students’ protest.  Federal police officers have beaten many students.

The University officials accused the local residents for supporting the protesters. Residents told ESAT’s reporter that they have seen students lying on the ground due to hunger.

The residents say, the actions of the students, who have not received any response to their queries, have been insightful.

መምህራንን ለመቆጣጠር መንግስት አዲስ አደረጃጀት ተግባራዊ አደረገ

መምህራን  እንደገለጹት አደረጃጀቱ ተግባራዊ በሆነባቸው በጎንደር በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የኢህአዴግ አባላት ከሆኑ ከመምህራን አንድ፣ ከተማሪዎች አንድ ከፖሊስ አንድ እንዲሁም ከወላጆች አንድ በትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኙ መምህራንን የቀን ተቀን እንቅስቃሴ፣ ፖለቲካ አመለካከት እና ሌሎችንም ተያያዥ ጉዳዮች ይከታተላሉ።
መመሪያው በሁሉም ትምህርት ቤቶች የወረደ ሲሆን፣ በአብዛኛው ትምህርት ቤቶች የአንድ ለአምስት አደረጃጀቱ ተግባራዊ ሆኗል።
በዚህ ድርጅት ውስጥ የሚመደቡት የኢህአዴግ አባላት ከተራው መምህር በላይ ስልጣን ያላቸው ሲሆን፣ መምህራንም እነሱን በመፍራት ሀሳባቸውን በግልጽ ለመናገር እየተቸገሩ ነው።
ኢህአዴግ በመላው አገሪቱ እየገነባ ባለው የአንድ ለአምስት  አደረጃጀት ህዝቡን ለመቆጣጠር ሙከራ ቢያደርግም እስካሁን ውጤታማ አለመሆኑን ገንባሩ ከወራት በፊት ባደረገው ጉባኤ መግለጹ ይታወቃል።

የቦሌ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን የድረሱልኝ ጥሪ አሰማች

የቦሌ ለሚ ቅ/ሩፋኤል የጻዲቁ አቡነ ኤዎስጣቲዎስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ብርሀን ተከስተ ካሳሁን “የድረሱልን ጥሪን ይመለከታል” በሚል ርእስ ለለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብጹዕ ወቅዱስ ፓትሪያርክ ረዳትና የጅማ ሀገረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ ለሆኑት ለ ብጹዕ አቡነ እስጢፋኖስ በጻፉት ደብዳቤ ላይ፣ የመንግስት ባለስልጣናት ቤተክርስቲያኑዋን በ7 ቀናት እንዲያፈርሱ እንዳዘዙዋቸው ተናግረዋል።
ደብዳቤው ” ቤተከርስቲያኑ ከተመሰረተ 4 አመታትን አስቆጠረ ቢሆንም በ2001 ዓም እንደማንኛውም አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተነስቶ ካርታውን በመጠባበቅ ላይ እንገኛለን። በተለይም የመንግስት አካላት በተለያየ ወቅት  ቦታው ድረስ እየመጡ፣ ቦታው የኢንዱስትሪ ቦታ ስለሆነ አፍርሱ የሚል ትእዛዝ በተደጋጋሚ ደርሶናል። አሁንም በቀን 12/02/2006 ኣም በመ/ቁጥር ቦ/ክ/ከ/መዝ/9539/06 በተጻፈልን ደብዳቤ ቦታው ለልማት ስለሚፈለግ ቤተ ክርስቲያኑን በ7 ቀን እንድታፈርሱ ሲል በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 አስተዳዳር የደምብ ማስከበር አገልግሎት ጽ/ቤት አሳውቆናል።” ይላል።
ደብዳቤው በማያያዝም “  የአካባቢው ህብረተሰብ አሁን በተረጋጋ መንፈስ የጸሎት ስነስርአትና አምልኮ ስነስርአት በሚፈጽምበት ወቅት በድጋሜ መጥተው በአስቸኳይ ቤተከርስቲያኑን እንድታነሱ የሚል ትእዛዝ ማስተላለፋቸው ምእመኑን እጅግ አሳዝናል ( አስቆጥቷል)። ስለሆነም ጉዳዩ ጊዜ የማይሰጥ ስለሆነ ለብጹእ ወቅዱስነታቸው ደብደቤ እንዲጻፍልንና ቅዱስነታቸውም ለክቡር አቶ ድሪባ ኩማ የአዲስ አበባ ከተማ አስተደዳደር ከንቲባ አስቸኳይ ደብዳቤ እንዲጽፉልን ስንል በቅድስት ቤተክርስያን  ስም እንጠይቃለን ብሎአል። ከደብዳቤው ጋርም የህዝቡን አቤቱታ የያዘ 10 ገጽ ወረቀት ተያይዞ ቀርቧል።
የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ደንብ ማስከበር አገልግሎት ጽ/ቤት በ12/02/06 ለሩፋኤል ቤተከርስቲያን በጻፈው ደብዳቤ ፣ ትእዛዙን የሰጠው የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት መሆኑን ጠቅሷል። በአቶ ጌታቸው አዲስ ፈለቀ የተጻፈው ደብዳቤ ቤተክርስቲያኑ በ7 ቀናት ውስጥ ካልተነሳ አስተዳደሩ ለሚወስደው እርምጃ ጽ/ቤቱ ሀላፊነቱን ይወስዷል ብሎአል።
የአዲስ አበባ ሀገረስብከትም ሆነ የፓትሪያርኩ ጽህፈት ቤት በጉዳዩ ላይ የሰጡት ምላሽ አልታወቀም።
የኦርቶዶክስ ሀይማኖት አንዳንድ አባቶች በቅርቡ መንግስት በቤተከርስቲያኑዋ ላይ እያደረሰ ያለውን ተጽእኖ መንቀፋቸው ይታወሳል።

tirsdag 29. oktober 2013

በአንድነት ፓርቲ በሰላማዊ ትግል ላይ እየተሰጠ ያለው ስልጠና በስኬት እንደቀጠለ ነው


በአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ክፍል የተዘጋጀውና በሰላማዊ ትግል ላይ ሰፊ ምርምር ባደረጉት በአቶ ግርማ ሞገስ በሰላማዊ ትግል ላይ እየተሰጠ ያለው ሳምንታዊ ስልጠና ቀጥሏል፡፡ በስልጠናው በሰላማዊ እና ትጥቅ ትግሎች መካከል ንጽጽራዊ ትንተና የተሰጠ ሲሆን ትንተናው በስድስት ክፍሎች የተከፋፈለ ነበር፡፡
የሰላማዊ ትግል እና የትጥቅ ትግል ልዩነቶች በመንግስት የፖለቲካ ኃይል ምንጮች (የስልጣን ምንጮች) ጥያቄ ዙሪያ፣ መንግስት በማስወገድ ጥያቄ ዙሪያ፣በመዓከል አመራረጥ ጥያቄ ዙሪያ፣በአደረጃጀት ጥያቄ ዙሪያ፣በስትራተጂያዊ ዘመቻዎች ጥያቄ 

ዙሪያ፣ትግሎቻቸውን በሚያራምዱባቸው መሳሪያዎች ጥያቄ ዙሪያ፣በመንግስት አመሰራረት ጥያቄ ዙሪያ፣በሞራል ጥያቄ ላይ ያላቸው ተቃርኖ፣ በፖለቲካ ባህል ጥያቄ ላይ ያላቸው ተቃርኖ፣በሰበኣዊ መብት ማክበር ጥያቄ ላይ ያላቸው ተቃርኖ፣ህዝብን በማቀራረብ፣ በማግባባት እና በአስታራቂነት ጥያቄ ላይ ያላቸው ተቃርኖ፣ህዝብን የራሱ ነፃ አውጪ በማድረግ ጥያቄ ላይ ያላቸው ተቃርኖ፣በዴሞክራሲ ሽግግር ጥያቄ ላይ ያላቸው አስተዋጽኦ ተቃርኖ እና ከአገር ጠላት አገሮች ጋር በመወዳጀት እና የአገር ሉዓላዊነትን በማስደፈር ጥያቄ ላይ ያላቸው ተቃርኖ በሰፊው ተብራርቷል፡፡
በስልጠናው ሰላማዊ ትግል እና ትጥቅ ትግል ተጋጋዥ ናቸው የሚለው አባባል ትክክል ነውን? የሚለው ነጥብ ሰፊ ትንተና ተሰጥቶበታል፡፡

የ“ሁለገብ የትግል ዘዴ” ማለት ምን ማለት ነው? ማድረግ ይቻላልን? በሚለውነጥብ ላይ ሰፊ ትንተና የተሰጠ ሲሆን ሁለቱን የትግል ስልቶች በጋራ መጠቀም እንደማይቻልና እጅግ ተፃራሪ መሆናቸውን አቶግርማ አብራርተዋል፡፡
ትጥቅ ትግል የመሳሪያ ቀላዋጭ እና የአገር ከሃዲ ያደርጋል፣ የአገር አንድነት ያናጋል፣ የአገር መፍረስ ያስከትላል፣ ሉዓላዊነትን ያስደፍራል፣ ከኢትዮጵያ ጠላት ጋር ያሻርካል። ከታሪካችን የተለቀሙ መረጃዎች፥ በማሰባሰብም
በአፄ ቴዎድሮስ ዘመን የተፈጸመ፣ ከ አፄ ቴዎድሮስ በኋላ እስከ ምኒልክ ዘመን የተፈጸሙ፣ በደርግ ዘመን የተፈጸሙ እንዲሁም ዛሬ ከኢሳያስ ጋር በመፈጸም ላይ የሚገኙ ስህተቶችን ተንትነዋል፡፡
በመጨረሻም በስልጠናው ሀሳብ ላይ መደምደሚያ ከተሰጠ በኋላ የስልጠናው ተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችን አንስተው በአቶ ግርማ ሞገስ ምላሽ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ስልጠናው በመጪው ቅሜም እንደሚቀጥል ታውቋል፡፡ ስልጠናው በቃሌ ፓልቶክ ሩም ውስጥም በቀጥታ ተላልፏል፡፡

የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ አስተዳደር ከተማሪዎች አመጽ ጀርባ ኢሳት እና ሌሎች ሀይሎች እንዳሉበት ገለጸ


ተማሪዎች  የርሃብ አድማ በማድረግ ላይ ሲሆኑ ዩኒቨርስቲው ትክክለኛነቱን አረጋግጦዋል፡፡
የተማሪዎች አመጽ የተነሳው መንግስት ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አዲስ የአለባበስ ፤ የአመጋገብ እና የአምልኮ  ስርዓት ህግ ማውጣቱን ተከትሎ ነው።  ” ተማሪዎች  እምነታችሁ ተው ፣ ማተባችሁን በጥሱ” ተብለናል ይላሉ።
በ2004 እና በ2005 ዓም ተማሪዎች ህጉን እንዲተገብሩ  ሙከራ ቢደረግም  ተማሪዎች ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ህጉ  ሳይተገበር ቀይቷል ሲሉ የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ንጉሴ ምትኩ ከክልል አመራሮች ጋር ባደረጉት ውይይት ተናግረዋል።
ተማሪዎች ለዘጋቢያችን እንደነገሩት ቁርስ፣ ምሳ እና እራት ለመመገብ በሀገሪቱ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የተፈቀደው የቀን በጀት  12 ብር ብቻ ነው፡፡ በደብረ ማርቆስ ከተማ 12 ብር አንድ ሻይ እና ዳቦ የመግዛት አቅም የሚሉት ተማሪዎች፣ መንግስት እየመገበን ሳይሆን የርሃብ አድማ ውስጥ እያስገባን ነው ይላሉ።
የተማሪዎችን ጥያቄ ትክክለኛነት የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ንጉሴ ምትኩ ያረጋግጣሉ፡፡ ተማሪዎች የሚቀርብላቸው የምግብ አቅርቦት የበጀት አነስተኛነት ከፍተኛ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ከመንግስት ፈቃድ ውጭ በሚልየን የሚቆጠር የበጀት ድጎማ እያደረግን ተማሪዎችን ለመመገብ ጥረት አድረገናል የሚሉት ፕሬዚዳንቱ፣ ሁኖም ግን መንግስት በገመገመውና በተቸው መሰረት የዳቦ ግራማቸው ከ80 ወደ 45 ግራም ዝቅ እንዲል መደረጉን ተናግረዋል፡፡
ተማሪዎች በ45 ግራም ዳቦ እና ከዚያ ባነሰ ሁኔታ ቁርሳቸውን እንዲመገቡ ተገደዋል፡፡ የዳቦው መጠን ግን ተማሪዎች አውጥተው ባስመዘኑት መሰረት ከ25- 30 ግራም የሚመዝን ሲሆን አንድ ጉራሻ የመሆን አቅም ብቻ ነው ያለው፡፡
በምግብ እጥረት ትምህርት በተጀመረ በወር ጊዜ ውስጥ 32 ተማሪዎች ታመው ወደ ህክምና ተቛማት መወሰዳቸውን ከጤና ጥበቃ የተገኘው መረጃ  ያመለክታል፡፡
የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ንጉሴ ምትኩ የተማሪዎች አመጽ የአመጋገብ እና የአምልኮ  ስርዓት የወጣውን ህግ ለማስተግበር በተካሄደው አሰገዳጅ ህግ እና በምግብ ማነስ ምክንያት በተነሳ ርሃብ ላይ ብቻ የተመሰረት ሳይሆን ኢሳት እና ሌሎች ሃይሎች ያደራጁት ሊሆን እንደሚችል፣ ኢሳት ዘገባውን ያቀረበበትን ሰአት አይቶ መናገር እንደሚቻል ገልጸዋል።
በአመጹ ሙሉ በሙሉ የስድስት ህንፃዎች መስታውቶች ወድመዋል፤ ሶስት የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አምቡላንሶችን ጨምሮ ከአገልግሎት ውጭ ሁነዋል፡፡
አመጹን የፌደራል ፖሊስ ለመቆጣጠር በወሰደው  እርምጃ በተማሪዎች ላይ ድብደባ ፈጽሟል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች ለአመጹ  ድጋፍ በመስጠታቸው ዬዩኒቨርስቲው መሪዎች ወቀሳ ሰንዝረዋል፡፡ነዋሪዎች በበኩላቸው ተማሪዎች እየራባቸው ሲወድቁ መመልከታቸውን ለደብረ ማርቆሱ ወኪላችን ነግረውታል፡፡ ተማሪዎቹ በተደጋጋሚ ጥያቄ አቅርበው መልስ በማጣታቸው በአጸፋው የወሰዱት  እርምጃ አስተማሪ መሆኑንም ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡

ባህር ዳር ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ሰራተኞቹን አባረረ

 
የባህር ዳር ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ሰራተኞች ባለፈው ነሀሴ ወር ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ በፋብሪካው አስተዳደር ላይ ያላቸውን ቅሬታ ገልፀው ነበር፡፡ ቦርዱ እና ማነጅመንቱ ሰራተኞቹን በመሰብሰብ መልስ እንደሚሠጡ ቃል ገብተው የነበረ ቢሆንም፣ ቃላቸውን በማጠፍ  በጥቅምት 15 ቀን 2006 ዓ.ም ሰራተኞቹን ለአመፅ አነሳስተዋል ተብለው የተፈረጁ 27 ሰራተኞች ከስራ አባረዋል ፡፡ በእለቱ የወጣው የማገጃ ደብዳቤ በፋብሪካው ስራ አስኪያጅ አቶ አባይ መላኩ ፊርማ የተጻፈ ነው።
የፋብሪካው ስራስኪያጅ ሰራተኞች መባረራቸውን አምነው ቁጥራቸው ግን 5 ብቻ ብለዋል፡፡ ስራ አስኪያጁ ሰራተኞቹ የተባረሩት  ምንም እውቅና የሌለው ህገ ወጥ የስራ ማቆም አድማ ስላደራጁ ነው ብለዋል

mandag 28. oktober 2013

TPLF’s Abay Dam Scam Failed again in Los Angeles

(Ethiopian Review) Woyannes (members of the ruling party in Ethiopia) by nature are among the most stupid creatures in the world. Why else would they come to the Diaspora to try to collect money from the same people they have forced into exile? And they do it over and over again even though every time they try, they are met with angry Ethiopians who confront them. Recently the Woyanne thugs were humiliated and chased away in Germany. Previously, they had attempted to do the same thing in Norway, Sweden, South Africa (where Tedros Adhanom ran like an impala when Ethiopians stormed his hotel), Houston, San Diego, Melbourne, and Dallas.
Yesterday, it was Los Angles. As expected, only about 10 – 20 people showed up to give them money (which is less than what they pay for organizing the fund raising event. Outside, several angry Ethiopians also waited for them.
A protest participant sent Ethiopian Review the following photos of Woyanne supporters arriving at the fund raising event. It is to be noted that many of these individuals are in the U.S. as political refugees, and yet they support the government that they claimed in their asylum application as their abuser. Why doesn’t the USCIS look into their fraudulent asylum application?
Woyanne thug shows middle finger to the protesters 
Los Angeles Woyanne agent 1
Los Angeles Woyanne agent 13
Los Angeles Woyanne agent 12

የወያኔን ሰላዮችን ከውጭ አለም ማጽዳት



    ከእስከ ነጻነት

    ኢትዮጵያ የነጻነት ቀንዲል ነች፡እንደ ስበሃት ነጋ ላሉ ባንዳ ወያኔዎች ግን ጣሊያንን አሸንፈን ለመላው የጥቁር ህዝብ የነጻነት ጎህ ቀዳጅ መሆናችን ኩራት ሳይሆን እፍረት ስለሚመስላቸው አገሪቷ ከነሰንደቅ አላማዋ ጥፍታ ማየት የዘወትር ጥረታቸው ነው፡ ሌት ተቅን የሚተጉትም ለዚህ ስለሆነ የኢትዮጵያዊነት ሰሜት ያላቸውን ሁሉ ማሰር፤ መግደል፤ ማጥፋት ዋና ትግባራቸው ነው፡ ይህም ተግባራቸው ከበረሃ እስከ አዲስ አበባ ከዛም ጎረቢት አገሮች ድረስ ዘልቆ አሁን ደግሞ ወደ ምእራብ ሐገራትም መጣሁ እያለ ነው።

    ግን አገሪቷም ሆነ ባንዲራዋ ልትጠፋ አትችልም፡ ለጥቁር ህዝብ የነጻነት ጎህ የቀደደች መሆኗን ለማረጋገጥ በርካታ ሃገራት ከቅኝ ግዛት ነጻ ሲወጡ ባንዲራቸውን መሰረት ያደረጉት በኢትዮጵያ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ ላይ ስለሆነ ባለም ዙሪያ ሲውለበለብ ይኖራል እንጂ ባንዳዎች እንደተመኙት ልትጠፋ አትችልም።

    ባለፈው አበበ ገላው ላይ የተቃጣው የግድያ ሴራ ከወያኔ አድሎአዊ አገዛዝ፤ ሸሽተን በመጣነው ሁሉ ላይ የተቃጣ ዛቻ ነው በሚል አጠር ያለች ጽሑፍ በእንግሊዘኛ ቋንቋ አቅርቤ ነበር። በዛሬው ጽሁፌ ማተኮር የምፈልገው ወያኔ (ለኔ ወያኔ ማለት ለአላማም ይሁን ለጥቅም የዚህን አገዛዝ እድሜ የሚያራዝም ሁሉ ነው) እንዴት ተሰደን ባለንበት አገር ለማስፈራራት ብርታቱን አገኘ? እንዴትስ የወያኔ አባላት ሰላዮች እና እበላ ባዮች በውጭው አለም በዙ? እንዴትስ መመንጠር እንችላለን የሚሉትን ዝርዝር ጉዳዮች በተመለከተ ይሆናል።

    ወደ ውጭ አገር መሰደጃ መንገዶች የታወቁ ናቸው፡ ከደርግ ጅምላ ፍጅት ሽሽት አገራቸውን ጥለው የተሰደዱ ብዙ ናቸው፡ በዘር የተደራጀው እና ዘር በማጥላላትና በማጥፋተ ላይ የተመሰረተው የወያኔ ቡድን ስርዓቱን በኢትዮጵያ ላይ ከጫነ ጀምሮ፡ ወያኔ በህዝቡ ላይ በሚያደርገው ጫና፤ ጭቆናና ግፍ አገራችንን ለቀን ተሰደናል፡ የተሳካልን ነጻው አለም ደርስናል ያልተሳካላቸው በበረሃ አሸዋ ተውጠው ቀርተዋል፡ ባህር ውጧቸዋል፡ ከቀይ ባህር እስከ ቬንዙዌላ የውሃ ጎርፍ ወስዷቸዋል፡ ከባህር እና ካሸዋ የተረፉት በየሀገራቱ እስር ቤቶች ተሰቃይተው ሞተዋል፡የውስጥ አካላቸው ተበልቶ ተወሰዷል፤ በእህቶቻችን ላይ የደረሰውንና እየደረሰ ያለውን ግፍ እና ስቃይ መናገር አይቻልም፡ የሰው ህሊና ሊያስበውና ሊሸከመው ከሚችለው በላይ ነው።

    እኛስ በዚህ መልኩ ተሰደድን የወያኔ ደጋፊዎች፤ እና ሰላዮችስ እንዴት መጡ?

    በስራ፤ በንግድ፤ ወይም በተለያየ መንገድ ከመጡት በተጨማሪ፡ እንደኛው ወያኔ ሊያኖረኝ አልቻለም፡ አሰረኝ፤ ገረፈኝ ብለው የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀው ውጭ የሚኖሩ በጣም ብዙ ናቸው፡ በሌላም በኩል ኤርተራዊ ነኝ፡ ብለው በኤርትራውያን ስም፤ ሱማሌያዊ ነኝ ብለው በሱማሌ ስም ጥገኝነት ጠይቀው የተፈቀደላቸው እንዳሉም ይታወቃል፡ እንዳውም የኤርትራውያንን ስደተኞች ተቀብያለሁ እና ሶስተኛ አለም ተረከቡኝ ብሎ ሶስተኛ አገሮች ከተረከቧቸው አብዛኛዎቹ የወያኔ ደጋፊዎች እና የወያኔ ሰላይ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ስደተኞችን ተቀባይ አገሮች አይወቁት እንጂ የህን ጽሁፍ በማንበብ ላይ ያለኸው፤ ያለሽው፡ ጠንቅቀው ያውቁታል።

    ለምን የወያኔ ደጋፊዎች፤ ወደ ነጻው አገር መጡ አደለም ጥያቄው፡ ይኸ መንግስት በድሎናል፤ ጨቁኖናል መኖር አልቻንም ብለው የጥገኝነት ጥያቄ አቅርበው፤ ጥያቄያቸው ተቀባይነት ካገኘ በሗላ ከዚሁ ጨቆነን ካሉት መንግስት ጋር አብሮ መስራት፤ የወያኔ ደጋፊዎች፤ ኢምባሲ ጭምር በሚያዘጋጁት ስብሰባ ላይ፤ የድጋፍ ሰልፍ ላይ እንዴት ሊገኙ ቻሉ?

    ይህ ብቻ አደለም ከድጋፍ አልፈው የወያኔ አገዛዝ አስመርሯቸው የተሰደዱትን በኬንያ፤ በዩጋንዳ በሱዳን፤ በሶማሊያ፤ በጅቡቲ ሲገሉ እና ሲያሰገድሉ ኖረዋል፡ ያንን ተግበር አሜሪካ፤ ካናዳ እና አውሰትራሊያም ሊሞከሩ እንደሚችሉ፤ መገመት በቻ ሳይሆን አበበ ገላው ላይ የተጠነሰሰው ሴራና የአሜሪካው የፌዴራል ምርምራ ቢሮ (FBI) ማክሸፉ ያላቸውን ዕብሪት በግልጽ ያሳያል።

    ይህ ደግሞ በአበበ ገላው ብቻ የሚቆም አደለም ለሌሎቻችንም የሚተርፍ የወያኔ ድግስ ነው ስለዚህ እንዴት ማስቆም አለብን የሚለው ነው ቁም ነገሩ።

    ይህንን ለማሰቆም ወይም የወያኔ ሰላዮችን አጋልጦ ለፍርድ ለማቅረብ የፖለቲካ ድርጅቶች ወይም የሲቪክ ድርጅቶች አያስፈልጉም፡ እነሱ ወያኔን ከስሩ ለመንቀል ይንቀሳቀሱ፤ ለዚህ ተግባር ግን የሚያሰፈልገው፡ በወያኔ የዘረኛ አገዛዝ ተማረህ የተሰደድክ፡ ግፋዊ አሰተዳደሩን መቋቋም አቅቶሽ አገርሽን ጥለሽ የወጣሽ፡ በወያኔ የግፍ ቀንበር እህትህን ያጣህ፤ ወንድምሽ እህትሽ በስደት ላይ እያሉ ባህር የዋጠብሽ፡ አንተ ነህ፤ አንቺ ነሽ የምታስፈልጊው፤ የምታስፈልገው። በአንድ ከተማ ውስጥ አንድ ወይም ሁለት ቁርጠኛ ኢትዮጵያዊ ካለ በቂ ነው፡ በኢትዮጵያ የህግ የበላይነት መከበር ጽኑ አላማ ያለውና በጥቅም ያማይገዛ ህሊና ያላቸው አንድ ወይም ሁለት ባንድ ከተማ ካሉ በጣምበቂ ነው፡ የሚጠበቀው መደባደብ ወይም መሰዳደብ አደለም የሚያሰፈልገው ወያኔ በድሎኛል ብሎ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቀ ሰው ከወያኔ ቡድን ጋር እየሰራ እና ኢትዮጵያውያንን እንዲሁም ጥገኝነት የሰጠውን አገር አየስለለ መሆኑን ሪፖረት ማረግ ብቻ ነው።

    ማንኛውም ሰው አንድ አገር የፖለቲካ ጥገኝነት ሲጠይቅ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በደለኝ ብሎ መኖር አልቻልኩም ካለና ጥያቄው ተቀባይነት ካገኘ በሗላ ያ መንግስት እስካልተቀየረ ድረስ ከዛ መንግሰት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ሊኖረው አይችልም፡ በምንም መልኩ ከዛ መንግስት ጋር ግንኙነቱን ከቀጠለ ከመንግስቱ ጋር ችግር የለበትም ማለት ነው ስለዚህ ወዳገሩ መመለስ አለበት፡ የኽ የኔ አስተያየት ሳይሆን የየሃገራቱ የስደተኛ ህጎች ናቸው።

    ስለሆነም ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቆ የተፈቀደለት፡ ወይም ኤርትራዊ፤ ሶማሊያዊ ነኝ ብሎ ጥገኝነት የተፈቅደለት (ወንድ ይሆን ሴት፤ አማራ ይሁን ኦሮሞ፤ ትገሬ ይሆን አደሬ፤ ማንም ይሁን ማ) የወያኔው ኢምባሲ በሚያዘጋጀው ፕሮገራም ላይ የሚሳተፍ፤ የወያኔ ባለስልጣናት በሚጠሩት ስብሰባ ላይ የሚገኝ፤ የወያኔ ደጋፊዎች ወይም ካደሬዎች በሚያዘጋጁት የወያኔ የድጋፍ ሰልፍ ላይ የሚገኘን፡ ከወያኔ ጋር የንግድ ስራ ጀምሮ ኢትዮጵያ የሚመላለስን ሁሉ ለሚመለከተው ክፍል ሪፖርት ማደረግ ያስፈልጋል።

    ባለፈው 21 አመት ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስት አልተቀየረም ስለሆነም በነዚህ ጊዜያት የወያኔ መንግስት በድሎኛል፤ ሊያኖረኝ አለቻለም ብሎ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቀ ሰው ሁሉ በምንም መልኩ ከወያኔ ጋር የሚሰራ፡ ወያኔ በሚያዘጋጀው ዝግጅት ላይ የሚገኝ ሁሉ ሪፖርት መደረግ አለበት።

    እዚህ ላይ አደራ የምለው እና ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ የሚገባው ሪፖርት የሚደረገው ነገር እውነት ብቻ እንዲሆን፤ በግል ቂም በቀል፤ ወይም በተወሰነ ዘር ላይ ያነጣጠረ እንዳይሆን አደራ እላለሁ፡፡ ወያኔን ያጠናከረው፡ የተወሰነ ዘር ወይም የወያኔው አባላት ብቻ ሳይሆን እበላ ባይ አጃቢ ጭምር መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡ ስለዚህ ሁሉም የወያኔን እድሜ እየለመነ የወያኔን ፍርፋሪ የሚለቃቅም ሁሉ ሪፖርት መደረግ አለበት።

    ወያኔን ለመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ ከወያኔ ጋር መደባደብ መነታረክ ሳይሆን ሰማቸውን ቢቻል አድራሻና ፎቶገራፋቸውን መዝግቦ መያዝ ነው ከዛ ለሚመለከተው ረፖርት ማድረግ።

    ሪፖርት ለማድረግ የግድ የግል ሰማችሁን መጠቀም አይኖርባችሁም፤ ሰሜ አይገለጽ ማለትም ትችላላችሁ፡ ከቤታችሁ ሪፖረት መላክ ካላመቻችሁ ወይም ካልፈለጋችሁ ከህዝብ መጻሕፍት ቤት ኮምፑተር ተጠቅማችሁ ሪፖርት ማድርግ ትችላላቸሁ፡ የህዝብ ቤተ መጻህፍት አባል ለመሆን ክፍያ አይጠይቅም ነጻ ነው፤ የሚጠይቀው መታወቂያ ወይም ባደራሻችሁ በስማችሁ የተላከ ደብዳቤ ብቻ በቂ ነው፡

    መልክታችሁ አጭር ነው፡

    “እገሌ የሚባል ሰው አዚህ አገር ሲገባ መንግስት ጨቆነኝ አላኖር አለኝ፤ ብሎ ነበር አሁን ግን ጨቆነኝ ከሚለው ከመንግስት ጋር በቀጥታ እየሰራ ስለሆነ ሰላይ ሊሆን ይችላል ወይም የጥገኝነት ጥያቄው የውነት አደለም ብዬ እጠራጠራለሁ ማጣራት ቢደረግ”

    ማጣራቱ የናንተ ጉዳይ ሳይሆን የደህንነት ሰራተኞች ጉዳይ ይሆናል፡ ከማንም ሳትማከሩ፤ አዩኝ አላዩኝ ብላችሁ ሳትፈሩ፤ ሚስጥሬ ይባክናል የሚል ስጋት ሳይኖራችሁ ትክክለኛውን መረጃ ለሚመለከተው ክፍል መስጠት የህሊና ነጻነት መጎናጸፍ እና የዜግነት ድርሻን መወጣት ነው፡

    ሪፖርት የምታደርጉባቸውም አድራሻዎች

    1. በዩናይትድ ሰቴትስ FBI (Federal Bureau of Investigation)https://tips.fbi.gov 2. በካናዳ Canadian Security Intelligence Service:http://www.csis-scrs.gc.ca/cmmn/cntcts-eng.asp 3. በአውስትራሊያ Australian security Intelligence Organization:http://www.asio.gov.au/Contact-Us.html እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይጠብቅ

    søndag 27. oktober 2013

    Religious leaders comment on the recent stern statements of EOTC

    Asked what the reasons for the unprecedented opposition and brave statements of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC) priests were last week, a religious leader said it could have to do with the change of the Patriarch.

    The difference so far had to do with the leader. The Patriarch himself was a supporter of the popes himself, the religious scholar said.

    Similarly, asked to what extent the Church and religious leaders will go to solve the problems, he said that he fears that the government could interfere and divert it.

    On the other hand, Aba Ameha Eyesus, one of the few priests who had been severly persecuted under the hands of the government, said the statements of the priests have come very late and are spoken out of anxiety.

    “After the Country has been destroyed, the national Flag has been disgraced and the physical and spiritual life of Ethiopians has been disturbed, they now have got the gut to speak just for the sake of feeling free from their fears” said Aba Ameha Eyesus.

    Stock of weapons found in the houses of 2 former TPLF officials

    According to Ethiopian law, an individual is permitted to hold a single licensed weapon. However, it is to be recalled that the government had in recent times been collecting weapons from all licensed and unlicensed gun holders in the name of weapon searches. During the 2005 election, the government had armed a certain ethnic group for self defence purposes, it was reported.
    This week, in the charges of the high profile corruption case of former Customs Director, Melaku Fenta et al., the prosecutor general said that it has found two Kalashnikovs, 2 pistols and one star pistol in total 9 weapons in the house of former Customs Deputy Director and official of the TPLF,  Gebrewahed Woldegiorgis. Similarly in the house of the other defendant, member of the TPLF and former top official of the National Intelligence, Woldeselassie W/Michael, two submachine guns, one Uzi submachine gun, one star pistol, one smoke bomb and different types of bullets were seized.
    It has been widely reported that Woldeselassie had a close relationship with Azeb Mesfin, the widow of the late Prime Minister, but was in grudge and fall outs with the Head of Ethiopian Intel, Getachew Assefa.
    Similarly, local newspapers have reported that the Court heard new accusations of adultery against Melaku Fenta. Melaku has been accused of using his governmental power to lure a married woman who came to his office seeking official assistance on taxation, to leave her husband and her three children and marry him. The prosecutors of the Federal Corruption Commission said Melaku abused his power to personally help Mekdes Lema and use public resources to adulterate her.
    The Commission’s prosecutors have also found that Sheikh Mohammed Hussein Al Amloudi’s MIDROC and the state owned Metal & Engineering Corp. (Metec), which is headed by General Kinfe Dagnew, were involved in corrupt practices including the import of untaxed goods. However, both companies and heads of the companies have not been sued.

    lørdag 26. oktober 2013

    ኢጣልያ፤ 700 ስደተኞች ከሞት ተረፉ









    በሌላ በኩል፤ የአዉሮፓ ሕብረት ስለ ሕገ ወጥ ስደተኛ ጉዳይ እየመከረ ባለበት፤ በአሁኑ ወቅት፤ ዛሬ በኢጣልያዋ ሲሲሊያ የባህር በር 700 ስደተኞች በባህር ወሰን ጠባቂዎች ከሞት  መትረፋቸዉ ተነገረ። የባህር ወሰን ጠባቂ ጓዶች 700 ዎቹን ስደተኞች በ24 ሰዓታት ጊዜ ዉስጥ ከአምስት የተለያዩ ጀልባዎች ማዳን ችለዋል። የባህር ድንበር ጠባቂዎች ከታደጓቸው ስደተኞች መካከል አብዛኞቹ ኤርትራዉያን መሃናቸው ተዘግቧል 

    በደቡብ ክልል የመምህራን ተቃውሞ እየተስፋፋ ነው

    መምህራን ለአባይ ግድብ ማሰሪያ በሚል  የመስከረም ወር ደሞዛቸው ያለፈቃዳቸው ተቀንሶ ከተሰጣቸው በሁዋላ የጀመሩት ተቃውሞ እየተስፋፋ መሆኑን ለኢሳት የሚደርሱት መረጃዎች ያመለክታሉ።
    የጨንጫ ወረዳ 7 ትምህርት ቤቶች መምህራን የተቆረጠው ደሞዛችን ካልተመለሰ ስራ አንሰራም በሚል አድማ ከመቱ በሁዋላ፣ በዛሬው እለት ደግሞ በጋሞጎፋ ዞን በምእራብ አባያ ወረዳ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራን ” የተቆረጠብን ደመወዝ የማይመለስ ከሆነ ስራ አንሰራም በሚል ” በስፍራው ለተገኙት ባለስልጣናት ተናግረዋል።
    የወረዳው አስተዳዳሪ፣ የወረዳው የድርጅት ጉዳይ ሃላፊና የወረዳው የመምህራን ማህበር ተወካይ በስፍራው ተገኝተው መምህሩን ለማወያየት የሞከሩ ሲሆን፣ መምህራኑ ግን ደሞዛችን ተመልሶ እስካልተሰጠን ድረስ ከእናንተ ጋር ለመወያየት ፈቃደኛ አይደለንም የሚል መልስ ሰጥተዋል።
    ባለስልጣናትም መምህራኑ ” አመጹን እንዲያቆሙ፣ የተቆረጠባቸው የመስከረም ወር ደሞዝ እንደሚመለስና በጥቅምት ወርም ያለ ፈቃዳችሁ እንደማይቆረጥባቸው”  ቃል ገብተው ለማረጋጋት ሞክረዋል።
    ባለስልጣናቱ መምህራኑን ይቅርታ በመጠየቅ ለማረጋጋት ቢሞክሩም፣ መምህራኑ ይቅርታውንም ለመቀበል ፈቃደኞች ሳይሆኑ ቀርተዋል ። ስለአባይ ግድብ ከእናንተ የተሻለ  በቂ መረጃ አለን በማለትም መምህራኑ በባለስልጣናቱ የቀረበውን ልመና ውድቅ አድርገዋል።
    በዚሁ ወረዳ የአይዶ አንደኛ ደረጃ፣ ወሌ አንደኛ ደረጃ፣ ምእራብ አንደኛ ደረጃ፣ ገልዶ አንደኛ ደረጃ እና የሌሎችም ትምህርት ቤቶች መምህራን የተቃውሞ ፊርማ አሰባስበው ለወረዳው ትምህርት ቤት ጽህፈት ቤት አቅርበዋል።
    ይህ በእንዲህ እንዳለ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ከምእራብ አባያ መሰናዶና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 15 የኢህአዴግ አባላት የሆኑ መምህራን ከድርጅት አባልነት ለመሰናበት የመልቀቂያ  ደብዳቤ አስገብተዋል። መምህራኑ ድርጅቱን ለመልቀቅ  ካቀረቡዋቸው መክንያቶች መካከል፣ “የኢኮኖሚ ችግር፣ የድርጅቱ ኢ- ዲሞክራሲያዊ ባህሪና በየጊዜው የሚፈጠርውን ጫና  ለመቋቋም አለመቻል” የሚሉ ይገኙበታል።
    ቀድም ብሎ በመሰናዶ ትምህርት ቤቱ ውስጥ 75 የኢህአዴግ አባላት መምህራን የነበሩ ሲሆን፣ 47 መምህራን ድርጅቱን በመልቀቃቸው 28 አባላት ብቻ ቀርተው ነበር። ከ28ቱ መምህራን መካከል ደግሞ ካለፈው ሰኞ ጀምሮ 15ቱ መምህራን የመልቀቂያ ደብዳቤ አስገብተዋል።

    torsdag 24. oktober 2013

    የአረና ትግራይ ቅሬታ



     አረና ትግራይ በተለያዩ ዞኖች በአባሎቹ ላይ ድብደባ እና እስራት እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ገልጿል። ድርጅቱ በፅሑፍ ባወጣው መግለጫ እና ለዶቸ ቬለ በሰጠው ተጨማሪ ማብራሪያ አረናን ለማዳከምና አሻንጉሊት ፓርቲ እንዲሆን ለማድረግ ጫና እና ወከባው ቀጥሏል ብሏል።
    አረና ትግራይ በተለያዩ ዞኖች በአባሎቹ ላይ ድብደባ እና እስራት እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ገልጿል። ድርጅቱ በፅሑፍ ባወጣው መግለጫ እና ለዶቸ ቬለ በሰጠው ተጨማሪ ማብራሪያ አረናን ለማዳከምና አሻንጉሊት ፓርቲ እንዲሆን ለማድረግ ጫና እና ወከባው ቀጥሏል ብሏል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር በበኩላቸው ወንጀል ፈፅመው ካልሆነ በስተቀር በፖለቲካ ፓርቲ አባልነት የሚታሰር የለም ማለታቸውን የአዲስ አበባ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር በጥንቅሩ ጠቅሷል።

    onsdag 23. oktober 2013

    አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ጠ/ሚ ኃይለማርያም ከማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አንድነት አሳሰበ::


    አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ካለፈው ስህተታቸው በመማር ከአጉልና ማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አሳሰበ።
    ፓርቲው ከትናንት በስትያ ባወጣው መግለጫ እንደገለፀው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ባለፈው ሳምንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በመሪ ደረጃ በማይጠበቅ መልኩ የአንድነትን እንቅስቃሴ ስም ለማጥፋት በመሞከራቸው ከዚህ ድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የራሳቸው አጀንዳ የላቸውም፣ የሻዕቢያ መልእክት አድራሾች ናቸው ያሉት የራሳችን አጀንዳ እንዳለን ጠፍቷቸው ሳይሆን ሆን ብለውና አቅደው ስም ለማጥፋት እንዲሁም ህዝቡ ውስጥ ጥርጣሬ ለመጫር በመፈለግ ነው ብሏል።
    ፓርቲው ተላላኪነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብና ይጠቅማል ብሎ ለቀረፃቸው የፖለቲካ ፕሮግራም ብቻ መሆኑን የገለፁ ሲሆን፤ እንዲህ አይነቱን ስም ማጉደፍም በቸልታ እንደማያልፈው ገልጿል። በተጨማሪም የሙስሊም ወገኖችን ጥያቄ በተመለከተ ፓርቲው በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ይመለስ፣ ዜጎች የመብት ጥያቄ ሲያነሱ መፈረጁ ይቁም እንዲሁም ካለአግባብ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ በማንሳታቸው ወደ እስር ቤት የተወረወሩ ዜጎች በአስቸኳይ ይፈቱ የሚል ጥያቄ ማንገቡን ፓርቲው ገልጿል። በመሆኑም ፓርቲው ከኢፍትሃዊት ጋር እንደማይደራደር እና እንደማይቀበለው አመልክቶ፣ ፓርቲውን ከሙስሊም ወገኖች ጥያቄ ጋር በማያያዝ ትርፍ ፍለጋ መሯሯጥ ወንጀል ነው ብሏል።
    ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሰላማዊ ሰልፍን በተመለከተ የተናገሩት በህገ መንግስቱ የተቀመጠውን መብት በአደባባይ የጨፈለቀ ነው ብሏል ፓርቲው። ሰላማዊ ሰልፍ ለሚያደርጉ በቂ ጥበቃ የለንም በሚል ተልካሻ ሰበብ የዜጎችን መብት መንጠቅ እንደማይቻል የገለፀው ፓርቲው፤ ጥበቃ ማድረግ ያልቻለ መንግስትም ስልጣኑን ለህዝብ በማስረከብ ይቅርታ ጠይቆ መሄድ እንጂ ከአሁን በኋላ መብታችሁን አታገኟትም ብሎ መዛት ትዝብት ላይ ይጥላል ብሏል።
    ፓርቲው አያይዞም የአፍሪካ መሪዎች ተሰብስበው አይ ሲሲ ሊከሰን አይገባም ሳይሆን ማለት ያለባቸው፣ የዜጎቻቸውን እንባ ማበስ እና ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲረጋገጡ መጣር ነው ብሏል። መሪዎች በርካታ መፍትሄ ፈላጊ ችግሮች ባሉባት አፍሪካ ተሰብስበው እንግደል፣ እንሰር፣ እንጨፍጭፍ፣ ዘር እናጥፋ፣ ዜጎቻችንን እናሰቃይ ግን መታሰርም፣ መከሰስም የለብንም የሚለው አቋም አሳፋሪ በመሆኑ ፓርቲው እንደማይቀበለው ገልጿል። በመሆኑም ዜጎች ላይ ግፍና ስቃይ የሚፈፅሙ ሁሉ ሳይውል ሳያድር ወደ ፍርድ መቅረብ አለባቸው በማለት፤ አንዳንድ የአፍሪካ መሪዎች አይሲሲን በተመለከተ የሚያራምዱትን የአትክሰሱን አቋም ፓርቲው እንደማይቀበለውም ገልጿል።

    አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ጠ/ሚ ኃይለማርያም ከማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አንድነት አሳሰበ

    አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ካለፈው ስህተታቸው በመማር ከአጉልና ማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አሳሰበ።
    ፓርቲው ከትናንት በስትያ ባወጣው መግለጫ እንደገለፀው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ባለፈው ሳምንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በመሪ ደረጃ በማይጠበቅ መልኩ የአንድነትን እንቅስቃሴ ስም ለማጥፋት በመሞከራቸው ከዚህ ድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የራሳቸው አጀንዳ የላቸውም፣ የሻዕቢያ መልእክት አድራሾች ናቸው ያሉት የራሳችን አጀንዳ እንዳለን ጠፍቷቸው ሳይሆን ሆን ብለውና አቅደው ስም ለማጥፋት እንዲሁም ህዝቡ ውስጥ ጥርጣሬ ለመጫር በመፈለግ ነው ብሏል።
    ፓርቲው ተላላኪነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብና ይጠቅማል ብሎ ለቀረፃቸው የፖለቲካ ፕሮግራም ብቻ መሆኑን የገለፁ ሲሆን፤ እንዲህ አይነቱን ስም ማጉደፍም በቸልታ እንደማያልፈው ገልጿል። በተጨማሪም የሙስሊም ወገኖችን ጥያቄ በተመለከተ ፓርቲው በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ይመለስ፣ ዜጎች የመብት ጥያቄ ሲያነሱ መፈረጁ ይቁም እንዲሁም ካለአግባብ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ በማንሳታቸው ወደ እስር ቤት የተወረወሩ ዜጎች በአስቸኳይ ይፈቱ የሚል ጥያቄ ማንገቡን ፓርቲው ገልጿል። በመሆኑም ፓርቲው ከኢፍትሃዊት ጋር እንደማይደራደር እና እንደማይቀበለው አመልክቶ፣ ፓርቲውን ከሙስሊም ወገኖች ጥያቄ ጋር በማያያዝ ትርፍ ፍለጋ መሯሯጥ ወንጀል ነው ብሏል።
    ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሰላማዊ ሰልፍን በተመለከተ የተናገሩት በህገ መንግስቱ የተቀመጠውን መብት በአደባባይ የጨፈለቀ ነው ብሏል ፓርቲው። ሰላማዊ ሰልፍ ለሚያደርጉ በቂ ጥበቃ የለንም በሚል ተልካሻ ሰበብ የዜጎችን መብት መንጠቅ እንደማይቻል የገለፀው ፓርቲው፤ ጥበቃ ማድረግ ያልቻለ መንግስትም ስልጣኑን ለህዝብ በማስረከብ ይቅርታ ጠይቆ መሄድ እንጂ ከአሁን በኋላ መብታችሁን አታገኟትም ብሎ መዛት ትዝብት ላይ ይጥላል ብሏል።
    ፓርቲው አያይዞም የአፍሪካ መሪዎች ተሰብስበው አይ ሲሲ ሊከሰን አይገባም ሳይሆን ማለት ያለባቸው፣ የዜጎቻቸውን እንባ ማበስ እና ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲረጋገጡ መጣር ነው ብሏል። መሪዎች በርካታ መፍትሄ ፈላጊ ችግሮች ባሉባት አፍሪካ ተሰብስበው እንግደል፣ እንሰር፣ እንጨፍጭፍ፣ ዘር እናጥፋ፣ ዜጎቻችንን እናሰቃይ ግን መታሰርም፣ መከሰስም የለብንም የሚለው አቋም አሳፋሪ በመሆኑ ፓርቲው እንደማይቀበለው ገልጿል። በመሆኑም ዜጎች ላይ ግፍና ስቃይ የሚፈፅሙ ሁሉ ሳይውል ሳያድር ወደ ፍርድ መቅረብ አለባቸው በማለት፤ አንዳንድ የአፍሪካ መሪዎች አይሲሲን በተመለከተ የሚያራምዱትን የአትክሰሱን አቋም ፓርቲው እንደማይቀበለውም ገልጿል።

    ONLF says it has attacked gov’t officials


    On an attack launched against the delegation of the Deputy Prime Minister of Ethiopia Demeke Mekonnen, nine regional leaders, domestic and foreign investors, who were visiting Ogaden Region last week, the Ogaden National Liberation Front (ONLF) said it has killed several Ethiopian troops at the airport and destroyed two vehicles.

    Hassan Abdualhi, Spokesperson of the Front, said to ESAT that the attack was launched as soon as delegates landed in Kebridahar town Airport last week.

    “We were already informed that the officials were coming to the Region so we were already prepared to execute the attacks” Hassan said.

    The Ethiopian government has not commented on the reports so far.

    It is to be recalled that artists and journalists had been sent to the Ogaden region to visit the “peace and developmental activities” there. 

    Sons of a politician afflicted

    eteran combatant of the TPLF and currently an opposition of the same Front said to ESAT that his children are going through difficult times.

    One of his sons, Yemane, has been disabled due to severe beating and torture in prison. Aehfom, his other son, has been imprisoned for the past seven months.

    Akbrom, a 10th grade student, has been seized from the field he was playing football has been arrested. Asgede said he had been able to visit him in prison after six daysapplying to officials.

    Asgede said “TPLF is now assaulting his children after me”.  He called every citizen to ply its part in saving the lives of his children.
    Asgede said Tigary region is has lost sleep, it is under darkness. Emigration,unemployment, lack of justice and corruption are rampant, he added.

    Religious leaders comment on the recent stern statements of EOTC


    Asked what the reasons for the unprecedented opposition and brave statements of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC) priests were last week, a religiousleader said it could have to do with the change of the Patriarch.

    The difference so far had to do with the leader. The Patriarch himself was a supporter of the popes himself, the religious scholar said.

    Similarly, asked to what extent the Church and religious leaders will go to solve the problems, he said that he fears that the government could interfere and divert it.

    On the other hand, Aba Ameha Eyesus, one of the few priests who had been severly persecuted under the hands of the government, said the statements of the priests have come very late and are spoken out of anxiety.

    “After the Country has been destroyed, the national Flag has been disgraced and the physical and spiritual life of Ethiopians has been disturbed, they now have got the gut to speak just for the sake of feeling free from their fears” said Aba Ameha Eyesus.

    የኢትዮጲያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግንባር መፍጠር

    0 ያህል የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይበልጥ ተባብረው በጋራ ለመታገል ያስችላቸው ዘንድ የጋራ ግንባር መፍጠራቸውን ኣስታወቁ።
     Die Gambia Street und Churchill Avenue führen schnurgerade auf das Rathaus der äthiopischen Hauptstadt Addis Abeba. Aufnahme vom Januar 2007. Foto: Peter Smolka +++(c) dpa - Report+++
    እነዚሁ ቀደም ሲል 33ቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይባል ይባል የነበረው ስብስብ አካል የነበሩ 10 ፓርቲዎች የፈጠሩት ጥምረት ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ወይንም በአጭሩ ትብብር ተብሎ ይጠራል ተብለዋል።
    አዲሱ ትብብር ከምርጫ ቦርድም የምዝገባ ማረጋገጫ ማግኝቱ ታውቀዋል
    ሰላሳ ሶስቱ ፓርቲዎች እየተባሉ የሚጠሩት ጥቅምት 15 ቀን 2005 ዓ ም በምርጫ ጉዳይ ላይ የአዳማውን ፒቲሺን የፈረሙ ፓርቲዎች ናቸው። ከእነዚሁ መካከል የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት ግን 24 ፓርቲዎች ሲሆኑ ካለፈው ጥቅምት 10 ቀን ወዲህ ደግሞ ወደ ቅንጅት ኣድገው ነበር።
    An Ethiopian woman casts her vote at a polling station in Addis Ababa, Ethiopia Sunday, May 15, 2005 during the third democratic elections in Ethiopia's 3,000-year history. (AP Photo/Karel Prinsloo)
    ባለፈው እሁድ በተካሔደው የጋራ ጉባዔ ላይ ደግሞ 10 ፓርቲዎች የመመስረቻ ጽሁፍ የመተዳደሪያ ደንብ እና መለስተኛ የድርጊት ፕሮግራም በመፈረም አቶ አለሳ መንገሻ የጌድኦ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ሊቀመንበር እና የአዲሱ ትብብር ኣስተባባሪ ኮሚቴ አባል ዛሬ ለዶቸቬሌ እንዳስረዱት ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ወይንም በአጭሩ ትብብር በሚል መጠሪያ መቀናጀታቸውን ኣውጀዋል።
    በእርግጥ የመድረክ አባል ድርጅቶች ለመቀናጀት ቴክኒካዊ ችግሮች ስላሉባቸው እንጂ ለመተባበር ዝግጁ መሆናቸውም ተጠቅሰዋል። መድረክ ውስጥ ያለው ቴክኒካዊ ችግር ደግሞ አቶ አለሳ እንደሚሉት መድረክ ግንባር በመሆኑ በመተዳደሪያ ደንባቸው መሰረት ኣንድ የመድረክ አባል ድርጅት ከሌሎች ድርጅቶች ጋር መዋሀድ እንጅ በትብብር ደረጃ መቀናጀት ስለማይችል ነው ተብለዋል። የመድረክ አባል ድርጅቶች የውስጥ ችግራቸውን ከፈቱ በአዲሱ ትብብር በኩል አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም አቶ አለሳ ኣስምረውበታል።
    የመድረክ አባል ድርጅቶችን ሳይጨምር በአዲሱ ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ውስጥ ካልተካተቱት መካከልም ስማያዊ ፓርቲን ጨምሮ የሲዳማ ህዝብ ዓርነት ንቅናቄ እና የጉራጌ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ይገኙበታል።
    ኣሁን ትብብር ፈጥረው እስከ መዋሀድ ልንሄድ እንችላለን የሚሉት ፓርቲዎች ኣንዳንዶቹ ኣገራዊ ፓርቲዎች ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ብሔራዊ ፓርቲዎች ናቸው። ይህንኑ ጉዳይ በማንሳት የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በኣንድ ወቅት እሳት እና ውሃ እንዴት አብሮ ለመስራት እንደሚስማሙ ኣይገባኝም ማለታቸው የሚታወስ ሲሆን አቶ አለሳ ግን በዚህ ኣይስማሙም።
    ምንም እንኩዋን የመጫወቻው ሜዳ ችግር እንዳለበት ቢገባንም በህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች ላይ ከኢህኣዲግ ጋር ልዩነት የለንም የሚሉት አቶ አለሳ መንግስት ህገ መንግስቱን እንዲያከብር ተስፋ ሳንቆርጥ እና ሳንታክት ታግለን ህዝባችንን ኣንቀሳቅሰን ለውጥ ለማምጣት እንሰራለን ብለዋል።