søndag 23. juni 2013

የሱዳኑ ፕሬዚዳንት የአባይ ግድብ ግንባታን እንደሚደግፉ አስታወቁ



ሱዳን ትሪቢውን እንደዘገበው ፕሬዚዳንት በሽር የግድቡ ግንባታ ለኤሌክትሪክ ሀይል ፍጆታ የሚውል በመሆኑ በግብጽም ሆነ በሱዳን የውሀ ፍጆታ ላይ የሚኖረው ተጽኖ አይኖርም ብለዋል።

ግድቡን ለመሙላት በሚያስፈልግበት ወቅት እንኳ በግብጽም ሆነ በሱዳን የውሀ ድርሻ ላይ ተጽኖ አያመጣም ብለዋል።
ፕሬዚዳንቱ ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ እንድትቀጥልም ጠይቀዋል።

ፕሬዚዳንት በሽር የሰጡት መልስ ግብጽና ሱዳን ቀድሞ የነበራቸው ጥብቅ ትስስር እየላላ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar