onsdag 17. desember 2014

የዞን 9 ጠበቃን ደብዳቤ ይዘናል

ከኦነግ እና ግንቦት 7 ጋር አብረው ሰርተዋል:: የሚል ክስ የተመሰረተባቸው ወጣት ጦማርያን ፍርድ ቤት በድጋሚ ቀርበው ነበር:: የቀረቡበት ምክንያት… የተጠቀሰው የወንጀል ዝርዝር እና አንቀጹ ተዛማጅ ባለመሆናቸው የጦማርያኑ ጠበቃ በክሱ ላይ ማስተካከያ እንዲደረግ ጠይቆ ነበር:: ጠበቃው ለፍርድ ቤት ካቀረቡት ደብዳቤ ውስጥ ገጽ 2 እና 3ትን ከዚህ  ቀጥሎ አቅርበነዋል::
zon9 bloggers
zon9 bloggers2
በፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ በሕቡዕ በመደራጀት፣ የወንጀል አድማ ስምምነት በማድረግ፣ በውጪ ኃይሎች በመደገፍና በማህበራዊ ድረ-ገፆች በመጠቀም እንዲሁም መንግሥት አሸባሪ ብሎ ከሚጠራው ግንቦት 7 እና ኦነግ ጋር በመተባበር ሁከትና ብጥብጥን ሊያስነሱ ሲንቀሳቀሱ ነበር በሚል የሽብር ወንጀል ክስ በመሠረተባቸው በእነሶሊያን ሽመልስ የክስ መዝገብ ላይ አሁንም በድጋሚ መጥራት ያለባቸው ጉዳዮች አሉ በሚል; ከላይ በተገለጸው አይነት የተከሳሽ ጠበቆች አቤቱታቸው በፅሁፍ አቅርበዋል።
ማኅሌትና ኤዶም በልደታው ካንጋሮ ፍርድ ቤት፡፡
ማኅሌትና ኤዶም በልደታው ካንጋሮ ፍርድ ቤት፡፡

zone9_2

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar