torsdag 15. juni 2017

ለሶስተኛ ጊዜ ተቀጥሮ የነበረው የባሕር ዳር የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የዋስትና መብት ጥያቄ ዳግም ውድቅ ተደረገ

ለዛሬ ሰኔ 7/2009 ዓ.ም ፡፡
(በሰማያዊ ብሔራዊ ሸንጎ የህዝብ ግንኙነት ንዑስ ኮሚቴ)
****************************************
«በከፍተኛ የአገር ሃብትና የሰው ህይወት ውድመት » ተጠርጥራችኃል በሚል አስር ወራቶች በእስር የቆዩት የሰማያዊ ፓርቲ የባህር ዳር አመራሮች ዳግም ያነሱት የዋስትና መብት ተነፍገው በባህር ዳር ማረሚየ ቤት እንዲቆዩ ሲል ፍርድ ቤቱ ዛሬ ከሰዓት በዋለው ችሎት ወሰነባቸው። በማረሚያ ቤት ሁናችሁ ጉዳያችሁን ተከታተሉ የተባሉት ታሳሪዎቹ “የትኛውን ጉዳይ” ብለው ቢጠይቁ ዳኛው መልስ እንደሌለው የተናገረው የታሳሪዎቹ ጠበቃ አዲሱ ጌታነህ
« የአንድ ምርመራ መዝገብ ማለቅ ያለበት በ15 ቀን ውስጥ ነው። ይህ ቀን በቂ አይደለም ከተባለ በፍርድ ቤት ተቀርቦ ተጨማሪ ቀናት ይጠየቃል እንጂ ምንም ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ባልተጠየቀበት ሁኔታ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩ ባለታወቀበት ምክንያት በማረሚያ ቤት ሁናችሁ ጉዳያችሁን ተከተተሉ ማለቱ አገሪቱ ያለችበትን ስር የሰደደ ህገ ወጥ የሆነና የህግ መሰረት የሌለው በተጨማሪም በአገሪቷ ላይ ፍትህ አልባነትና ምን ያህል እንደነገሰ አመላካች ድርጊት ነው ብሏል።» ፓርቲውን ለማዳከም ሲባል ብቻ ክስ ሳይመሰረትባቸው ከአስር ወራቶች በላይ ታስረው መራራ መስዋትነት ካለ ምንም ጥፋታቸው እየከፈሉ ያሉት አመራሮች አቶ ማሩ ዳኘው፣ አቶ መልካሙ ታደለ፣ አቶ ሲሳይ ታከለ፣ አቶ እጅጉ አስማረ እና አቶ ወርቁ ጥላሁን ናቸው።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar