torsdag 16. mai 2013

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ የተጀመረው ተቃውሞ ለሁለተኛ ቀን ቀጥሎአል




በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ጋሞ ካምፓስ ትናንት ከምሽቱ 4 ሰአት ላይ የተጀመረው ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ ያዋለ ሲሆን “ተማሪዎች መብታችን ይከበር፣ ድምጻችን ይሰማ፣ ጥያቄያችን ይመለሰ፣ ተምሮ ለኮብል ስቶን ” የሚሉ መፈክሮች አሰምተዋል።

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፌደራል ፖሊስ አባላት ግቢውን የተቆጣጠሩት ሲሆን ተማሪዎች እርስ በርስ እንዳይገናኙ አድረገዋል።

ተማሪዎች የምግብ መበላሸትን ሰበብ አድርገው አድማውን ቢጀምሩም፣ ሌሎች ከትምህርት ጥራት እና ከአስተዳደር ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን ማነንሳታቸውን አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የዩኒቨርስቲው ሰራተኛ ተናግረዋል።

 እስካሁን 9 ተማሪዎች ታስረዋል። የተደበደቡ ወይም ሌላ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች እስካሁን ለማግኘት አልቻልንም።
ተማሪዎች በየክፍላቸው መስኮቶች ላይ ቆመው ጥያቄያችን እስካልተመለሰ ድረስ ትምህርት አንጀምርም በማለት እየጮሁ ነው።
በጉዳዩ ዙሪያ የትምህርት ቤቱን አስተዳዳሪዎች ለማግኘት ያደረግነው መኩራ አልተሰካም።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar