onsdag 4. desember 2013

ኢህአዴግ ለግንቦት7 ያቀረበው የእንደራደር ጥያቄ የተለያዩ አስተያየቶችን እያስተናገደ ነው

በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚኖሩ ዜጎች በስልክ እየሰጡ ባለው አስተያየት  ግንቦት7 ከኢህአዴግ ጋር መነጋገሩን አይደግፉም። አብዛኞቹ የሚሰጡት ምክንያት ደግሞ “ኢህአዴግ ተዳክሟል፣ ኢህአዴግ የሚታመን ድርጅት አይደለም” የሚሉ ናቸው። በዚህ ዙሪያ ኢትዮጵያውያን የሰጡት አስተያየት የሚከተለውን ይመስላል
በሌላ በኩል ደግሞ የተወሰኑ ኢትዮጵያውያን የድርድሩ ዜና መልካም ወሬ መሆኑን ለኢሳት በላኩት የኢሜል መልክት አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉም ፓርቲዎች በሰላም ተነጋግረው ለአገራቸው ቢሰሩ መልካም መሆኑን የጠቀሱት እነዚህ አስተያየት ሰጪዎች ድርድሩ ከልብ የመጣና ኢህአዴግ እውነተኛ ለውጥ ለማምጣት ዝግጁ ከሆነ፣ ለአገሪቱ መልካም ዜና ነው ብለዋል።
ኢህአዴግ ለግንቦት7 የድርድር ጥያቄ ማቅረቡን መዘገባችን  ይታወቃል። ግንቦት 7 በተለያዩ ምክንያቶች የቀረበለትን  ድርድር ሳይቀበለው ቀርቷል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar