mandag 30. desember 2013

የጋዜጠኞችና የጋዜጠኝነት ይዞታ በኢትዮጵያ

በአሁኑ መንግሥት ሳንሱር ሲነሳ የግል ጋዜጦች ቁጥር ከፍ ቢልም በሂደት ግን ቁጥራቸው አሽቆልቁሎ አሁን በጣት የሚቆጠሩ ብቻ ቀርተዋል ፤ ከ1997 ምርጫ ወዲህ የጋዜጠኞች መከሰስ መታሰርና ከሀገር መሰደድ ተባብሷል ። ለዚህም በምክንያትነት የሚነሱት የሃገሪቱ የፕሬስና የፀረ ሽብር ሕግ ናቸው ።
በኢትዮጵያ ጋዜጠኝነት በየስርዓቱ ባጋጠሙት ልዩ ልዩ እንቅፋቶች ሰበብ የሚጠበቅበትን ሚና መጫውት እንዳልቸለ የመስኩ ባለሞያዎች ያስረዳሉ ። ባለሞያዎች እንደሚሉት ለዚህ አብዩ ምክንያት ሙያው በተለይ በየስርዓቱ የሚደርስበት ፖለቲካዊ ጫና ነው ። በኢትዮጵያ በቀደሙት ሁለት መንግሥታት መገናኛ ብዙኃን በሳንሱር ማነቆ ስር ነበር የሚሰሩት። በአሁኑ መንግሥት ሳንሱር ሲነሳ የግል ጋዜጦች ቁጥር ከፍ ቢልም በሂደት ግን ቁጥራቸው አሽቆልቁሎ አሁን በጣት የሚቆጠሩ ብቻ ቀርተዋል ፤ ከ1997 ምርጫ ወዲህ የጋዜጠኞች መከሰስ መታሰርና ከሃገር መሰደድ ተባብሷል ። ለዚህም በምክንያትነት የሚነሱት የሃገሪቱ የፕሬስና የቨረ ሽብር ሕግ ናቸው ። የጋዜጠኞችና ሰነ ምግባር እና የሙያ ብቃት ጉድለትም በሀገሪቱ ጋዜኝነት ተገቢውን ድርሻ ላለመወጣቱ በምክንያትነት ይጠቀሳሉ ። እንወያይ በኢትዮጵያ የጋዜጠኞችና የጋዜጠኝነትን ይዞታ ይቃኛል ። ተወያዮቹ የሬፖርተር ጋዜጣ አዘጋጅ የማነ ናግሽና የቀድሞው የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጅ መስፍን ነጋሽ ናቸው ።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar