lørdag 31. januar 2015

የሚሊዮኖች ድምጽ ጋዜጣ (ቁጥር 5)

የሚሊዮኖች ድምጽ ጋዜጣ በየሳምንቱ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ እየታተመ ለህዝብ የሚቀርብ ጋዜጣ ነው። ጋዜጣው በዚህ ሳምንት እትሙ የሚከተሉትን አበይት ጉዳዮችን ይዟል።
-‹‹የፈሰሰው ደምና የተሰበረው አጥንት ለነጻነት የተከፈለ ዋጋ ነው›› -የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በላይ በፍቃዱ ፕሬዝዳንት
-መንግሥት መሸኛው ደርሷል!  – እሱም ይሄን ያውቃል!
“በውንብድና የሚቆም የነፃነት ትግል አይኖርም!” ነብዩ ሃይሉ
አቶ ኤርሚያስ ለገሠ/ የቀድሞ የመንግሥት ጉዳዮች ኮሙኑኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ/ ደግሞ ለሚሊዮኖች ድምጽ ልዩ ቃለ ምልልስ ሰጥተዋል። ከተናገሯቸው ዋና ዋና ነገሮች መካከል የሚከተሉት አንኳር ጉዳዮች ይገኙባቸዋል።
‹‹ሀገራችን መስቀለኛ መንገድ ላይ ቆማለች››
‹‹ለኢትዮጵያ ህዝብ፣ በተለይም ለአዲስ አበባ ህዝብ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››
‹‹ምርጫ ቦርድ በህወሃት ቁጥጥር ሥር ያለ ተቋም ነው። የሰው ኃይሉን ምደባና ቅጥር ያደረግነው እኛ ነን››
‹‹ወዳጄ ሽመልስ ከማል 90 በመቶ ጊዜውን የሚያጠፋው በጋዜጦች ላይ እንከን በመፈለግ ነበር››
‹‹አልፎ አልፎም ለፍትህ ሚኒስቴር የክስ ቻርጅ የሚያዘጋጀው ሽመልስ ከማል ነበር››
‹‹አንድነቶች በምንም መልኩ መደናገጥ የለባቸውም›› ይላሉ። ከአቶ ኤርሚያስ ጋር የተደረገውን ሙሉውን ቃለ ምልልስ በዚህ እትም ላይ ያገኛሉ።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar