mandag 16. februar 2015

ኣቶ ገብሩ ኣስራት የምርጫ ካርድ ተከለከሉ..!


ዓረና-መድረክ ወክለው በመቐለ ምርጫ ክልል ለፌደራል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ የሆኑት ኣቶ ገብሩ ኣስራት “የመራጭነት ካርድ ጨርሰናል” በሚል ምክንያት ተከልክለዋል።

ይህ የሆነው እሁድ የካቲት 06 / 2007 ዓ/ም ከቀኑ 10 ስዓት በመቐለ ኣስራ 15 ቀበሌ እንዳባ ኣነንያ ምርጫ ጣብያ በኣካል ተገኝተው በጠየቁበት ወቅት ነው።

የምርጫ ካርድ በመቐለ ምርጫ ጣብያዎች ከሓሙስ 28 / 05 / 2007 ዓ/ም ጀምሮ ሲሆን ከዚህ ቀን በሗላ የመራጭነት ካርድ ማግኘት ኣልተቻለም።

የትግራይ ምርጫ ፅህፈት ቤት ችግሩ እንዳጋጠመ ያመነ ሲሆን ለችግሩ መፍትሄ ግን ሊያበጅ ኣልቻለው።

 ይህ ችግር ያጋጠመው በየምርጫ ጣብያው “ከእቅድ በላይ በመቶዎች ካርድ በመወሰዳቸው መሆኑ” ያስረዳሉ የጣብያዎቹ ሰዎች።
ይህ የህወሓት ወጣትና ሴቶች ሊግ ኣባላት እስከ ሰዎስት የመራጭነት ካርድች በተለያዩ ቦታዎች እያውጡ መሆኑ ታውቋል።

 የህወሓት መንግስት የትግራይ ሰዎች A.B.C.D ብሎ በመመደብ ካርዱ ለ A.B ቅድምያ በመስጠት እንዳስፈላጊነቱ ደግሞ C ለተሰጣቸው ሰዎች ካርዱ ይሰጣቸዋል።

Dየተመደበው ዜጋ የተለያዩ ምክንያቶች በመስጠት ካርድ እንዳይ ደርቸው እየተደረገ ነው።
በዚህ ለሚመርጥህ ሰው ለይተህ ካርድ በመስጠትና ለታማኝ የሊግ ኣባላት ከ3 በላይ ካርድ በማደል ከወዲሁ የምርጫው ውጤት ለመወሰን ጥረት እየተደረገ ነው ያለው።

ማንኛውም ሰው በኣቅራብያው ያለው የምርጫ ጣብያ ጠይቆ ካርድ መኖሩ ኣለመነሩ ማረጋግጥ ይችላል።

 ይህ ማጭበርበርያ ዘዴ ለማውጣት የተፈለገበት ዋነኛ ምክንያት የትግራይ ህዝብ እንደማይመርጣቸው በማረጋገጣቸው ነው።
ኣሁንም ምርጫ ቦርድ የመራጭነት ካርድ እንዲልክና የህዝቡን ፍላጎት እንዲያከብር እንመክራለን።
ኣቶ ገብሩ ኣስርትም የመራጭነት ካርድ ሊሰጣቸው ይገባል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar