torsdag 26. november 2015

አቶ አብርሃም ጌጡ ይግባኝ ተጠየቀበት

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በአቶ ማሙሸት አማረ ካቢኔ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የውጭ ጉዳይ ኃላፊ የነበረው አቶ አብርሃም ጌጡ ህዳር 14/2008 ዓ.ም አራዳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት (ሰባራ ባቡር) ቀርቦ ይግባኝ ተጠይቆበታል፡፡ የአራዳ ምድብ ችሎት ለህዳር 11/2008 ዓ.ም ቀጥሮበት የነበር ቢሆንም ህዳር 7/2008 ዓ.ም ፍርድ ቤቱ በነፃ እንዲለቀቅ መወሰኑ ይታወቃል፡፡
አቶ አብርሃም ጌጡ ሰኔ 12/2008 ዓ.ም ቤቱ ተበርብሮ ከታሰረ በኋላ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ ቆይቷል፡፡ ወደ ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ተዛውሮ ከቆየ በኋላ ከሀምሌ 12/2008 ዓ.ም ጀምሮ ማዕከላዊ ታስሮ ይገኛል፡፡ አቶ አብርሃም ጌጡ ‹‹በሽብር ወንጀል›› ለ6ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ከተያዘበት ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ መዝገቦችና በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ለ11ኛ ጊዜ መቅረቡን ጠበቃው ገልፀዋል፡፡
አቶ አብርሃም ጌጡ ወደ ማዕከላዊ ተዛውሮ ለሶስት ወራት በማዕከላዊ የቆየው ‹‹በሽብር ወንጀል›› ነው ተብሎ የነበር ቢሆንም ፍርድ ቤቱ የተከሰሰው በሽብር ሳይሆን በሀሰት ወሬ በማውራት በመሆኑ፣ ይህም ዋስትና እንደማያስከለክል፣ ለዚህ ክስም በቂ ዋስትና አስይዞ እንዲለቀቅ ወስኖ ነበር፡፡ ይሁንና አቶ አብርሃም ጌጡ ከእስር እንዲለቀቅ ፍርድ ቤቱ ከወሰነ በኋላም በማዕከላዊ እስር ቤት ታስሮ እንዲቆይ ተደርጎ ከሰባት ቀናት በኋላ ህዳር 14/2008 ዓ.ም ይግባኝ ተጠይቆበታል፡፡ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ህዳር 16/2008 ዓ.ም ድረስ ‹‹የሀሰት ወሬ በማውራት›› በሚል ክስ ቀርቦበት እንዲፈታ የተወሰነለት አቶ አብርሃም ጌጡ በማዕከላዊ ታስሮ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar