onsdag 5. november 2014

በውጥረት የተጀመረው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ በሰላም ተጠናቀቀ

በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ2007 የሚደረገው የጥቅምት ወር የቅዱስ ሲኖዶስ ጠቅላላ ጉባዔ በሰላም እና በስምምነት ተጠናቋል። ቀደም ሲል ማህበረ ቅዱሳንን ለማሳጣት እና በአሸባሪነት ለመወንጀል፤ በፓትርያርኩ አማካኝነት በተጠራው ስብሰባ ላይ ክፋት ያለው ንግግር ሲያደርጉ የነበሩ ሰዎች ቤተ ክርስቲያናዊ ቅጣት ደርሶባቸዋል። ፓትርያርኩም ቢሆኑ፤ በመጨረሻ የቅዱስ ሲኖዶሱን ወቀሳ ተቀብለው፤ “እሺ ከናንተ ቃል አልወጣም።” ይበሉ እንጂ፤ ለዚህ ሁሉ የዳረጋቸውና ልዩ ጸሃፊያቸው የነበረው ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ እንዲባረር የሚል ሃሳብ ሲቀርብ “እኔን ብታባርሩኝ ይሻላል፤ በፍጹም አይሆንም።” በማለታቸው ለግዜው የልዩ ጽሃፊያቸውን ጉዳይ ወደጎን በመተው በሌሎቹ የቤተክርስቲያኗ አማሳኞች ላይ ቅጣት አሳልፈው ጉባዔው በሰላም እና በጸሎት ሲከናወን ነበር የሰነበተው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት

የቅዱስ ሲኖዶሱን የስብሰባ ሂደት በቅርብ ይከታተል የነበረው “ሐራ ዘተዋሕዶ” የተባለው ድረ ገጽም የጉባዔውን የመጨረሻ ውሎ ዘግቧል። በኛ በኩል የመግለጫውን ኮፒ አስቀድመን፤ ከዚያ በመቀጠል ለዝርዝር ዘገባው የ”ሐራ ዘተዋሕዶ”ን ሙሉ ዜና መልሰን ለናንተ አቅርበነዋል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ጋዜጣዊ መግለጫ
የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ጋዜጣዊ መግለጫ

የቅዱስ ሲኖዶስ ዓመታዊ ምልአተ ጉባኤ ተጠናቀቀ

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar