onsdag 28. oktober 2015

የመኢአድ ሕጋዊው ፕሬዝዳንት አቶ ማሙሸት አማረ የአሜሪካ ቪዛ ተከለከሉ

ህብር ሬዲዮ ( ላስ ቬጋስ) የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) ሕጋዊው ፕሬዝዳንትና በአገዛዩ ምርጫ ቦርድ ህገ ወጥ ውሳኔ ከቢሮ የተባረሩትና በቅርቡ ከእስር በነጻ የተፈቱት አቶ ማሙሸት አማረ በውጭ ከሚገኙ የፓርቲው ደጋፊዎች ጋር ለመነጋገር ወደ አሜሪካ አቅደውት የነበረው ጉዞ በዛሬው ዕለት ቪዛ በመከልከላቸው ሳይሳካ መቅረቱን ለህብር ሬዲዮ የፓርቲው ምንጮች የላኩልን መረጃ ያስረዳል።

 አቶ ማሙሰት አማራ ግብኖት 5 ቀን 2008 ከመንገድ ላይ በአገዛዙ ደህነቶች ታፍነው ከአራት ወራት በላኢ በተሌኤዩ እስር ቤቶች ሲንገላቱ የቆዩ ሲሆን በፓርቲው ውስጥ ከፕሮፌሰር አስራት ሊቀመንበርነት ጊዜ ጀምሮ ሲያገለግሉ የቆዩና በምርቻ 97 ከቅንጅት መሪዎች ጋር የታሰሩትን ጨምሮ በመረጡት ሰላማዊ ትግል ሳቢአያ ለስምንት ጊዜአት ታስረዋል። አገዛዙ መቶ በመቶ አሸነፍኩ ካለበት ምርቻ ዋዜማ መኢአድና አንድነት ያካሄዱትን ሕጋዊ ጉባዔ በምርቻ ቦርዱ አማካይነት ድጋሚ እንዲደረግ ሲያስገድድ ከመላው አገሪቱ የተሰባሰቡ የመኢአድ የጠቅላላ ጉባዔን በቀናት ልዩነት በድጋሚ ጠሩ ሲሆን ለሁለተኛ ጊዜ ፓርቲውን
Mamushet_Amare_us_embassy_02
በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ መመረጣቸው ይታወሳል። የአገዛዙ ምርጫ ቦርድ የፓርቲውን ጉባዔ ውሳኔ በመሻር ቢሮውን በፖሊስ ቁጥጥር ስር በማድረግ አቶ ማሙሸትና ዛሬ በእስር ቤት የሚገኙትን የፓርቲውን የውጭ ግንኙነት ሀላፊና ሌሎች አመራሮችንና ውሳኔውን ያልተቀበሉትን አባላት አባሮ በምትካቸው ስልታኔን ለቅቄአለሁ ያሉትን ቀድሞ የፓርቲው ፕሬዝዳንት አቶ አበባው

መሐሪን ከቤታቸው በማምታት ቦርዱ ስልታን ላይ በማስቀመጥ ግለሰቡ ከማን ጋር ሲሰሩ እንደቆዩ ችምር ያጋለጠ ውሳኔ ነው ሲሉ የፓርቲው ሰዎች መግለጻቸው አይዘነጋም። አቶ ማሙሰት ቦርዱን ለፈጸመው ሕገ ወጥ ውሳኔ በፍርድ ቤት ክስ የመሰረቱት ቢሆንም ክሱ ዳር ሳይደርስ ግንቦት 5 ቀን 2008 ከቤታቸው አቅራቢያ በአገዛዙ ደህነቶች ታፍነው መጀመሪያ ቦሌ ምድብ ፖሊስ ጣቢያ

መታሰራቸው እና በሊቢያ በኤይሲስ የተቀሉና የተገደሉ ኢትዮጵአውያን ሐዘናቸውን በገለጹበት ወቅት ተገኝተህ አመጽ ቀስቅሰሀል የሚል ክስ ቀርቦባቸው የደህነት አባላት ቀርበው በሀሰት ከመሰከሩ ድርጊቱን መስቀል አደባባይ ተገኝተው ፈጽመዋል በተባሉበት ሚአዚያ 14 ቀን 2008 በቦታው እንዳልነበሩ፣ በዕለቱ ምርቻ ቦርድን ከሰው ልደታ ፍርድ ቤት ክርክር ላይ እንደነበሩ ከፍርድ ቤት

ማረጋገጫ አቅርበው፣በዕለቱ አብረዋቸው ፍርድ ቤት የነበሩ ጓዶቻቸውን አስመስክረው ፍርድ ቤቶ ክሱ ተቋርጦ በነጻ ይለቀቁ ቢላቸውም ሳይፈቱ ከእስር ቤት ወደ እስር ቤት መዛወራቸውን መዘገባችን ይታወሳል። አቶ ማሙሸት አማረ ከእስር ከተፈቱ በሁዋላ ለህብር ሬዲዮ በሰጡት ቃለ ምልልስ ከዚህ በሁዋላ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ብታደርግ እንገድልሃለን መባላቸውንና የደህነቶች ክትትል

ከወቱም በሁዋላ እንዳልተቋረጠ ነገር ግን እስኪገሉኝ ሰላማዊ ትግሉን እቀጥላለሁ ማለታቸው ይታወሳል። አቶ ማሙሸት አማረ የመኢአድ ሕጋዊው አመራር እና ብዙሃኑ አባላት በምርቻ ቦርድ ሕገ ወጥ ውሳኔ ቢራችን ቢነጠቅም ተመልሰን ትግሉን እንቀጥላለን ሲሉ ከዚህ ቀደም በሰጡት ቃለ ምልልስ የገለጹ ሲሆን የሰሞኑ የአሜሪካ ጉዞዋቸው ከፓርቲው ደጋፊዎች ጋር ለመነጋገር የታቀደ ሲሆን በኤምባሲው ቪዛ ክልከላ ሳቢያ ጉዟቸው ተስተጓጉሏል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar