torsdag 8. oktober 2015

የላይ አርማጭሆ ገበሬዎች በህወሓት አገዛዝ ፌደራልና ልዩ ኃይል ፖሊሶች በገፍ እየታፈሱ ወደ እስር ቤት እየተጋዙ ነው






የላይ አርማጭሆ ገበሬዎች በህወሓት አገዛዝ ፌደራልና ልዩ ኃይል ፖሊሶች በገፍ እየታፈሱ ወደ እስር ቤት እየተጋዙ ነው፡፡ ዘረኛው እና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ ከፌደራል ፖሊስ፣ ከልዩ ኃይል እና ከመከላከያ ተመርጦ የተውጣጣ ሰራዊት በላይ አርማጭሆ በሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች ማለትም በሙሴ ባንብ በጃኒካው፣ በገንበራ እና በሌሎች በርካታ አካባቢዎች ያሰራጨ ሲሆን ከሦስቱ ክፍሎች የተጣመረው ኃይል በየገበሬው መንደር ተሰግስጎ በማሸበር በመሳሪያ ገፈፋና በአፈሳ ተግባራት ላይ በሰፊው ተሰማርቶ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በላይ አርማጭሆ ገንበራ ቀበሌ ብቻ • አቶ አራጋው አበራ(የሚሊሻ ኮማንደር የነበረ) • አቶ አወቀ ጎሉ • አቶ ተቀባ ብርሃን • ወጣት ቴዎድሮስ ሙሉ • ወንድሙ ሙሉ እና • ወይዘሮ ደብሬ የኔዓለም የተባሉ ገበሬዎች ታፍነው ተወስደዋል፡፡ እነኚህን ስማቸው የተዘረዘሩትን ጥቂት ድሃ ገበሬዎች ጨምሮ በአገዛዙ የታጠቁ ኃይሎች በየቀኑ ከቀያቸው እየታፈኑ የሚወሰዱት ሰዎች በትክል ድንጋይ ልዩ ኃይል የጦር ካምፕ ውስጥ ታጉረው እደሚገኙ ተገልጿል፡፡

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar