mandag 30. juni 2014

እንደ ከሳሾቼ 100 ሺ የማከራየው ቤት የለኝም” ሲሉ አቶ ገብረውሃድ ተናገሩ

መንግስት በሙስና ወንጀል የከሰሳቸው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ የቀድሞዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ እና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ገብረ ዋህድ ወልደጊዮርጊስ የእምነት ክህደት ቃላቸውንለፌዴራልከፍተኛፍርድቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት የሰጡ ሲሆን፣ አቶ ገብረውሃድ “በኢትዮጵያቴሌቪዥን 16 ቤትአለውተብሎበካሜራተቀርፆመነገሩየሚያሳዝንመሆኑን ፣ እርሳቸውበአዲስአበባውስጥአንዲትጐጆእንደሌላቸውና ቢኖራቸው ኖሮ ልጆቻቸው መጠለያ እንደማያጡ ተናግረዋል።
‹‹እንደከሳሾቼ 100,000 የማከራየውቤትየለኝም፤›› በማለት ንጽህናቸውን ለማስረዳት የሞከሩት አቶ አቶ ገብረውሃድ፣ ከሳሾቼ ያሉዋቸውን ሰዎች  በስም ከመጥቀስ ተቆጥበዋል።
ሪፖርተር እንደዘገበው  አቶ ገብረውሃድ መሬት  መቀበላቸውንነገር ግንቤትለመሥራትአቅምስለሌላቸውምእንዳልሠሩበትዘግቧል።
ዋና ዳይሬክተሩ አቶ መላኩ ፋንታ በበኩላቸው ” ልንመሰገንበት በሚገባ ስራ ወንጀለኞች መባላችን ያሳዝናል ” ሲሉ የቀረበባቸውን ክስ ክደዋል።
“አቶመላኩከገቢያቸውጋርየማይመጣጠንከ3.2 ሚሊዮንብርበላይየሆነንብረትናገንዘብአፍርተዋል”በሚልለቀረበባቸውክስ፣እንደማንኛውምሰው 175 ካሬሜትርቦታላይቤትመሥራታቸውን፣ይህደግሞለእሳቸውብቻተነጥሎወንጀልሊሆንእንደማይችልገልጸው፣ ዓቃቤሕግየቤቱንግምትአሳስቶማቅረቡንምተናግረዋል።
ዓቃቤ ሕግ እንደ ክሱ ያስረዱልኛል ያላቸውን ምስክሮቹን ከሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ አቅርቦ እንዲያሰማ ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ ሰጥቷል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar