onsdag 23. januar 2013

የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ግቢአቸውን ለቀው ወጡ

    


             በባህርዳር ዩኒቨርስቲ ስር በሚገኙት በፔዳ ፣ ፖሊ፣ ይባብና ዘንዘልማ ካምፓሶች ይማሩ የነበሩ ከ95 በመቶ ሙስሊም ተማሪዎች ግቢአቸውን ለቀው መውጣታቸውን የተወሰኑትም ወደ መጡበት አካባቢ መመለሳቸውን ተማሪዎች ገለጹ።

 ተማሪዎቹ ግቢአቸውን በመልቀቅ ትምህርታቸውን ለማቋረጥ የወሰኑት ከሶስት ሳምንት በፊት የግቢው አስተዳዳሪዎች በዩኒቨርስቲው ውስጥ የሚደረግ ጸሎት እንዲቆም፣ ሴቶች ጂሃብም ኒቃምብ እንዳይለብሱ መከልከላቸውን ተከትሎ ነው።

አንዳንድ ተማሪዎች ከትናንት ጀምረው ትምህርት በማቋረጥ ተቃውሞአቸውን ሲገልጹ የነበረ ቢሆንም፣ የዩኒቨርስቲው አስተዳዳሪዎች “ትእዛዙ ከበላይ አካል የመጣ ነው ምንም ማድረግ አንችልም” የሚል ምላሽ መስጠታቸው ተማሪዎች ግቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። አንድ ተማሪ እንደገለጸው የተወሰኑ ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው መመለሳቸውን ፣ ሌሎችም ትኬት በመቁረጥ ላይ ናቸው።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar