torsdag 31. januar 2013

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ አንዲት ተማሪ ራሱዋን መጸዳጃ ውስጥ በመግባት አጠፋች



ገነቴ ጌታቸው የተባለችው ተማሪ መጸዳጃ ቤት ውስጥ ራሱዋን በመወርወር ያጠፋቸው ባለፈው ሳምንት ነው።

 በትምህርቷ ከፍተኛ ውጤት የነበራት ተማሪ ገነቴ ራሱን ለማጥፋት ለምን እንደወሰነች በትክክል ለማወቅ ባይቻልም ተማሪዎች እንደሚሉት ከሶስት ሳምንት በፊት የግቢው ተማሪዎች የውሀ፣ የመጸዳጃ እና ሌሎች አገልግሎቶች አልተሟሉልንም በሚል ተቃውሞ ከማስነሳታቸው ጋር ሊያያዝ ይችላል።

 ተማሪዎቹ ቤተሰቦቻቸውን በማስቸገር በሚላክላቸው ገንዘብ የፕላስቲክ ውሀ ሲገዙ መቆየታቸውን ያወሱት የሟቿ ባልደረቦች፣ ይሁን እንጅ ተማሪዋ የመጣችበት ቤተሰብ ይህን ለሟሟላት ባለመቻሉ ተማሪዋ በችግር ውስጥ ትገኝ ነበር ብለዋል።

 አሟሟቷንም ከገንዘብ ችግር ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ጠቁመዋል።

ትምህርታቸውን አቁመው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢያቸው ተመልሰው መደበኛ ትምህርት የጀመሩ ቢሆንም፣ የፌደራል ፖሊስ አባላት ግን አሁንም በዩኒቨርስቲው አካባቢ በብዛት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ለማወቅ ተችሎአል::


የቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ አስተዳዳሪዎችን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar