onsdag 24. april 2013

በወልድያ ከተማ በርካታ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ታሰሩ



በመላው አገሪቱ ከሚካሄደው የሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በወልድያ ከተማ 10 ሙስሊም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከአለፈው አርብ ጀምሮ መታሰራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል።

በዛሬው እለትም እንዲሁ አንድ የሁለተኛ ደረጃ እንግሊዝኛ መምህር የሆኑት አቶ አብደላ እና የመደርሳ ትምህርት ቤት የእቃ ግምጃ ቤት ሀላፊ የሆኑ ግለሰቦች ተይዘው ታስረዋል።

መንግስት የሙስሊሙን እንቅስቃሴ ለማፈን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተቃውሞው አስተባባሪዎች ናቸው የሚላቸውን ሰዎች እየያዘ በማሰር ላይ ይገኛል። የተያዙት ተማሪዎች በአሁኑ ጊዜ በወልድያ እስር ቤት ውስጥ ይገኛሉ።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar