tirsdag 30. april 2013

በተለያዩ የአለም ክፍሎች መንግስት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው



ለባይ ግድብ መዋጪ ለማሰባሰብ በኖርዌይ ኦስሎ የተጠራው ስብሰባ ለሁለተኛ ጊዜ በአገሪቷ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንዲቋረጥ ተደርጓል።

በተመሳሳይ ሁኔታም በካልፎሪኒያ ሳንዲያጎ ለአባይ ግድብ ማሰሪያ ተብሎ የተጠራው ስብሰባ በአካባቢው በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ተቃውሞ ሰብሰባው እንዲቋረጥ ተደርጓል።

በሌላ በኩል ደግሞ በኔዘርላንድስ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በአማራ ተወላጆች ላይ የሚፈጸመውን የማፈናቀል ዘመቻ አውግዘዋል።


 የኢትዮጵያውያን ማህበር በሆላንድ ትናንት በአምስተርዳም ከተማ በጠራው ስብሰባ የህወሀት ኢህአዴግ አገዛዝ በቤንሻንጉል

 ጉሙዝና እና በሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰውን ግፍ ፣ በእስር ቤት ውስጥ በሚገኙ የህሊና እስረኞች ላይ የሚደርሰውን እንግልት እንዲሁም በሙስሊሙና በክርስቲያኑ ላይ የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ለአውሮፓ መንግስታት ለማሳወቅ ሜይ 15፣ 2013 በአውሮፓ ህብረት መቀመጫ በሆነችው ብራሰልስ የተቃውሞ ሰልፍ ማዘጋጀቱን አስታውቋል።

በሌላ ዜና ደግሞ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት የጠራው ስብሰባ በጀርመን ተካሂዷል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar