torsdag 11. april 2013

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የመብራት እና ውሀ እጥረት አማረረን ይላሉ



በአዲስ አበባ መብራት ለተከታታይ ሶስት ቀናት ማግኘት ትልቅ ዜና እየሆነ ነው የሚለው ዘጋቢያችን፣ የመብራት መቋረጥን ተከትሎ በሚፈጠረው ችግር ባንኮች፣ አየር መንገዶችና ሌሎች ድርጅቶች ስራቸውን በተገቢው መንገድ ለመስራት እንዳልቻሉ ገልጿል።

ኢትዮጵያ ለጅቡቲ የኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ መጀመሩዋን የተናገረው መንግስት፣ መብራትን በፈረቃ ለማቅረብ መዘጋጀቱንም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በመብራት እጦት ብቻ ሳይሆን በውሀ ችግርም እየተሰቃዩ ነው፡፡ አንዳንድ አካባቢዎች ካለፉት ሶስት ቀናት ጀምሮ ውሀ አላገኙም።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar