onsdag 19. august 2015

በአማራ ክልል አንዳንድ ዞኖች አርበኞች ግንቦት 7ንና ትህዴንን ትደግፋላችሁ በሚል እስራትና ድብደባ እየደረሰባቸው ነው


በአማራ ክልል የሚገኙ አንዳንድ ዞኖች ላይ የሚኖሩ ንፁሃን ዜጎችን የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ የተቃዋሚ ድርጅቶችን ትደግፋላችሁ በሚል እስራትና ከፍተኛ ድብደባ እየደርሰባቸው መሆኑ ታወቀ። የደህሚት ድምጽ ደረሰኝ ባለው መረጃ እንዳመለከተው በክልሉ አንዳንድ ዞኖች ላይ የሚኖሩ ዜጎችን ከፌድራል የደህንነት መስሪያ ቤት የተላኩ ደህንነቶች ንፁሃን ዜጎችን የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ ድርጅቶችን እየደገፋችሁ ወጣቶችንም ወደ አርበኞች ግንቦት 7ና ትህዴን እየላካችሁ ነው በሚል የሃሰት ውንጀላ እየደበደቡና እያስፈራሩ መሆኑን የገለፀው መረጃው እንደዋና መነሻነትም የኢሳትን ቴሌቪዥንና የተቃዋሚዎችን ሬዲዮ ስታዳምጡ ተገንታችኋል የሚል መሆኑን አስረድቷል። በክልሉ የአምባገነኑ መንግስት ተላላኪነት የሃሰት ውንጀላ ከደርሰባቸው መካከል በአዊ ዞን አንከሻ ጓጉሳና ጃዊ ወረዳዎች በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ሰከላና ወምበርማ ወረዳዎች በሰሜን ወሎ ዞን መቄትና ዋድላ ወረዳዎች የሚገኙ ንፁሃን ዜጎችን እያሰቃዩ ናቸው::

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar