tirsdag 11. august 2015

የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት መግለጫ አወጡ

ቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት፤ በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር ተበትነው እንደሚገኙ ይታወቃል። በውጭ አገር የሚገኙት እነዚህ የሰራዊቱ አባላት በቅርቡ ባደረጉት ስብሰባ፤ በቅርቡ በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላይ የተሰጠውን ውሳኔ ተቃወዋል። ዘረኛው የኢህአዴግ መንግስት ላለፉት 24 አመታት በህዝባችን ጫንቃ ላይ ተንሰራፍቶ በመቀመጥ እያደረሰ ያለውን መከራ መዘርዘር ግዜ ማባከን መሆኑን የገለጸው ይኸው መግለጫ፤ ህዝቡ ይህንን አምባገነን ስርአት ለማስወገድ በሰላማዊ መንገድ ለማካሄድ ቢሞክርም የህዝቡን ትግል እንደፍርሃት በመቁጠር ከፍተኛ ንቀት በማሳየታቸው ህዝቡ ወዳላስፈላጊ የትግል አቅጣጫ አምራቱን፤ መግለጫው አብራርቷል።
መግለጫው በማጠቃለያው ላይ፤ በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ የተሰነዘረውን ዘመቻ በመቃወም የቀድሞው የሰራዊቱ አባላት ከህዝቡ ጎን በመቆም የዜግነት ግዴታቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar