onsdag 12. august 2015

መንግስት በሕዝብ የተመረጠው ቴዲ አፍሮን በስነጥበብ ዘርፍ ለመሸለም ፍላጎት እንደሌለው በይፋ አሳየ


በየዓመቱ የሚካሄደና ዘንድሮም ለ3ኛ ጊዜ ነሐሴ 30 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ ካፒታል ሆቴል በሚከናወነው ‹የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት› በየዘርፉ የተመረጡ የመጨረሻዎቹ አምስት ዕጩዎችን መንግስት ልክ እንደምርጫው አጭበርብሮ ራሱ የሚፈልጋቸውን ሰዎች አስቀመጠ:: ካለፈው ታህሳስ ወር ጀምሮ በተሰጠው የሕዝብ ጥቆማ የዓመቱ በጎ ሰው በሚል በስነጥበብ ዘርፍ ዝነኛው ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ምርጫን ቢያገኝም መንግስት በምርጫው እንደማጭበርበር እንደለመደው በፖለቲካዊ ውሳኔ ከ እጩዎች ዘንድ እንዳይካተት መደረጉ ተጋልጧል:: ከታኅሣሥ ወር ጀምሮ በተሰጠው የሕዝብ ጥቆማ መሠረት ታሪካቸውና ሥራቸው ተሰብስቦ፣ በበጎ ሰው ሽልማት የምርጫ ሂደት ኮሚቴ የተመረጡት 45 ዕጩዎች ናቸው ብሎ መንግስት ካስቀመጣቸው ሰዎች መካከል ሁሉም መንግስት ራሱ እንዲሸለሙልኝ እፈልጋለሁ ያላቸውን እንዳጨ የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል:: ቴዲ አፍሮ በስነጥበብ የዓመቱ በጎ ሰው ዘርፍ የበርካታ ሕዝብ ድምጽን ቢያገኝም ከ እጩዎች ዝርዝር እንዲወጣ ተደርጓል:: ዘንድሮ መንግስት 9 ሰዎችን በሕዝብ ምርጫ እሸልማለሁ ቢልም ቅሉ ምርጫው ለመንግስት ፖለቲካ ቅርበት ያላቸው ሰዎችን የሚያካትት እንጂ ትክከለኛው የሕዝብ ጥቆማ እንዳልሆነ ታማኝ ምንጮች ይናጋራሉ:: ሕወሓት የሚመራው መንግስት በሕዝብ የተጠቆሙ ሰዎችን ትቶ በራሱ መንገድ ሕዝብ መረጣቸው ብሎ ያስቀመጣቸው ሰዎች ዝርዝራቸው የሚከተለው ነው፡፡ በ2007ዓም በልዩ ልዩ ዘርፎች ዕጩ የሆኑ በጎ ሰዎች በሳይንስ ምርምር ዘርፍ ዕጩዎች 


1. ፕ/ር ኢ/ር አበበ ድንቁ (አአዩ)
2. ኬሚካል መሐንዲስ ጌታሁን ሄራሞ
3. ዶክተር አበበ በጅጋ
4. ፕሮፌሰር አሥራት ኃይሉ
5. ዶ/ር ይርጉ ገ/ሕይወት (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል) በሥነ ጥበብ ዘርፍ ዕጩዎች
1. አቶ አለ ፈለገ ሰላም
2. እማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩ
3. አቶ ተስፋየ አበበ(የክብር ዶክተር)
4. ሰዓሊ ታደሰ መስፍን
5. አባተ መኩሪያ በበጎ አድራጎት ዘርፍ ዕጩዎች
1. ወ/ሮ አበበች ጎበና
2. አቶ አስመሮም ተፈራ /ሲኒማ ራስ አካባቢ የተቸገሩትን የሚረዳ/
3. ስንታየሁ አበጀ (የወደቁትን አንሱ) እንጦጦ ማርያም አካባቢ)
4. አቶ አስፋው የምሩ /የአሠረ ሐዋርያት ት/ቤት መሥራች/ ዊንጌት አካባቢ
5. ትርሐስ መዝገበ በቢዝነስና ሥራ ፈጠራ ዘርፍ ዕጩዎች
1. አባ ሐዊ /አቶ ገብረ ሚካኤል (በትግራይ ክልል ለአብርሃ ወአጽብሐ አካባቢ ገበሬዎች ሥራ የፈጠሩ ገበሬ)
2. ሰላም ባልትና
3. አዋሽ ባንክ
4. ካፒቴን ሰሎሞን ግዛው
5. ካልዲስ ቡና በቅርስና ባሕል ዘርፍ ዕጩዎች
1. አቶ ዓለማየሁ ፋንታ
2. አቶ ሀብተ ሥላሴ ታፈሰ
3. አቶ ዓለሙ አጋ
4. EMML /HMML(የኢትዮጵያ የብራና መጻሕፍት ማይክሮ ፊልም ድርጅት)
5. ማኅበረ ቅዱሳን በማኅበራዊ ጥናት ዘርፍ ዕጩዎች
1. ፕ/ር ሪቻርድ ፓንክረስት
2. ደሳለኝ ራሕመቶ
3. ዶክተር ፈቃደ አዘዘ
4. ፕሮፌሰር ሺፈራው በቀለ 5. ፕሮፌሰር በላይ ካሣ በጋዜጠኛነት ዘርፍ ዕጩዎች
1. አቶ መዓርጉ በዛብህ
2. አቶ ያዕቆብ ወልደ ማርያም
3. አቶ ነጋሽ ገብረ ማርያም
4. ታምራት ገብረ ጊዮርጊስ(ፎርቹን ጋዜጣ)
5. ቴዎድሮስ ጸጋየ በስፖርት ዘርፍ ዕጩዎች
1. አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው
2. መምህር ስንታየሁ እሸቱ (ከበቆጅ ብዙ አትሌቶች እንዲወጡ ያደረገ መምህር)
3. መሠረት ደፋር
4. ኢንስትራክተር ሽፈራው እሸቱ
5. ዶክተር ወ/መስቀል ኮስትሬ መንግሥታዊ ኃላፊነትን በብቃት በመወጣት ዘርፍ ዕጩዎች 1. አቶ ግርማ ዋቄ(የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩ)
2. አቶ መኮንን ማን ያዘዋል
3. አቶ ሽመልስ አዱኛ
4. ዐማኑኤል የአእምሮ ሕክምና ሆስፒታል
5. ኢንጅነር ስመኘው በቀለ

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar