tirsdag 16. juli 2013

በአዲስ አበባ የአንድነት ፓርቲ አባሎች እየታሰሩ ነው








ፓርቲው በደሴና እና በጎንደር የተሳኩ የተቃውሞ ሰልፎችን ባካሄደ ማግስት ከ30 በላይ አባሎቹ በዋና ከተማዋ የተቃውሞ ፊርማ ሲያሰባስቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል።

ባለፉት ሳምንታትትም በተመሳሳይ መንገድ የታሰሩ እና የፍርድ ቤት ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ያሉ አባላት አሉ።

አንድነት ፓርቲ ለ3 ወራት በሚቆየው የተቃውሞ እንቅስቃሴ  በዋና ዋና ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን ከማካሄድ ባሻገር ቤት ውስጥ ስብሰባዎችንና እና 1 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን ፊርማ ያሰባስባል።

ፓርቲው በደሴና በጎንደር ያደረገው ተቃውሞ ለፓርቲው አባላት ከፍተኛ መነቃቃት እንደፈጠረ አንዳንድ አባላቱ ተናግረዋል።




Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar