onsdag 17. juli 2013

የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ከናይጀሪያ ለቀቁ




የአፍሪካ ህብረት በጤና ጉዳይ ላይ ለመመካከር በናይጀሪያ ባዘጋጀው ስብሰባ ላይ የተገኙት የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር አልበሽር ሰብሰባቸውን ሳይጨርሱ ወደ አገራቸው የተመለሱት ፣ አለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የናይጀሪያ መንግስት ይዞ እንዲያስራቸው አቤቱታውን ለፍርድ ቤት ካቀረበ በሁዋላ ነው።

ፕሬዚዳንቱ ሰኞ እለት ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ በድንገት አገሪቱን ለቀው መውጣታቸው ታውቋል።

ፕሬዚዳንት በሽር ናይጀሪያ ሲገቡ የናይጀሪያ መንግስት የክብር አቀባበል አድርጎላቸው ነበር።  የናይጀሪያ አለማቀፍ የወንጀለኞች ፍርድቤት ጥምረት ፕሬዚዳንቱ ታስረው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ለአገሪቱ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ክስ መስርቶ እንደነበር ዘገባዎች አመልክተዋል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar