onsdag 3. juli 2013

ሩሲያ ተዋጊ ጄቶችን ለኢትዮጵያ ለመሸጥ እየተደራደረች ነው


አር አይ ኤ የተባለው የዜና ማሰራጫ የሮስቦሮን ኤክስፖርት አርምስ ምክትል ዳይሬክተር የሆኑትን አሌክሳንደር ሚካሄቨን ጠቅሶ እንደዘገበው ሩሲያ 18 ኤስ ዩ 30 ከ የተባሉ የጦር ጄቶችን ለኢትዮጵያ ለመሸጥ በድርድር ላይ ናት።

ጄቶችን ለመሸጥ ከኢትዮጵያ ጋር እየተነገጋገርን ነው። የጄቶችን ቴክኒካዊና ታክቲካዊ ብቃት ከፍ ለማድረግ እንዲሁም ከአየር ወደ ምድር የሚወነጨፉ ሚሳኤሎችን እንዲሸከሙ ለማድረግ ሀሳብ አቅርበናል። ብለዋል ምክትል ዳይሬክተሩ።

የኢትዮጵያ መንግስት ስምምነት ላይ ከደረሰ ዘመናዊ ጄቶችን በሚቀጥሉት 4 ወይም 6 ወራት ውስጥ እንደሚያቀርቡ ባለስልጣኑ ገልጸዋል።

ዘገባው የጄቶቹን ዋጋ አላስቀመጠም።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar