onsdag 19. februar 2014

77ኛው የኢትዮጵያ ሰማእታት ቀን ተከብሮ ዋለ


ኢትዮጵያውያን በጣሊያን ወራሪ ሃይል በግፍ የተጨፈጨፉበት ቀን በመላው አለም በሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየተዘከረ ነው።
በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የሰምአታት ሃውልት ጀግኖች አባት አርበኞች በተገኙበት በአሉ ተከብሯል።
የካቲት 12፣ 1929 ዓም አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም የተባሉ ኢትዮጵያውያን ግራዚያኒን ለመግደል የጣሉትን ቦንብ ተከትሎ፣ የጣሊያን ወራሪ ሰራዊት በወሰደው እርምጃ  ከ30 ሺ በላይ ኢትዮጵያውን መገደላቸው ይታወቃል።
በ5 አመቱ የጣሊያን ወረራ  ወቅት አእላፍ አእላፍ የኢትዮጵያ ጀግኖች ወረራውን በመቃወም ሲዋጉ በጀግንነት መውደቃቸው ይታወቃል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar