torsdag 20. februar 2014

በሱዳን በጎረምሶች የተደፈረችው ኢትዮጵያዊት በድንጋይ ተወግራ ልትገደል ትችላለች ተባለ


ዘጋርድያን እንደዘገበው የ18 አመቷ ወጣትና ነፍሰጡሩዋ ኢትዮጵያዊት በዝሙት ተግባር በመከሰሷ በድንጋይ ተወግራ ልትገደል እንደምትችል የምስራቅ አፍሪካ የሴቶች ስትራቴጂክ ኔትወርክ ወይም ሲሃ የተባለውን ድርጅት በመጥቀስ ዘግቧል። የ9 ወር ነፍሰ ጡሩዋ ወጣት በእስር ቤት ውስጥ ያለምንም ምንጣፍ በባዶ ኮንክሪት ላይ እንደምትተኛ ጋዜጣው ዘግቧል።
ኢሳት ከወር በፊት ዜናውን ይፋ ባደረገበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ መንግስት የሱዳን ኢምባሲ የዲያስፖራ ዘርፍ ሃላፊ ሆኑት አቶ….ወጣቱዋ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ ገልጸው ነበር።
ይሁን እንጅ ጋርዲያን እንደሚለው ፣ ወጣቱ የ3 ወር ነፍሰጡር እያለች በ7 ጎረምሶች መደፈሩዋን ወዲያውኑ ለፖሊስ ብታመለክትም፣ ፖሊስ ግን የኢድ አል ፈጥርን በአል ሰበብ በማድረግ አቤቱታዋን ሳይቀበላት ቀርቷል።
ወጣቱዋ ዝሙት አለመፈጸሙዋንና ተገዳ መደፈሩዋን ብትናገርም ተሰሚነት አላገኘችም። የሱዳን ፍርድ ቤት የአገሪቱን ፖሊስ ገጽታ ለመጠበቅ ሲል እንዲሁም ጥፋተኞችም ለመታደግ ሲባል ንጹዋን ወንጀለኛ አድርጎ ማቅረቡ አሳሳቢ መሆኑን ሲሃ መግለጹን ዘጋርድያን ዘግቧል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar