tirsdag 18. februar 2014

ሎንዶን፤ የኢትዮያዊዉ የሳይበር ጥቃት ክስ




ብሪታኒያ የሚገኙ ኢትዮጵያዊ፤ የኮምፒዉተራቸዉን ፕሮግራም በመጥለፍ የሚጠረጥሩትን የኢትጵያን መንግሥትን እርምጃ እንዲመረምር የብሪታንያን ፖሊስ ጠየቁ።

 አቶ ታደሰ ከርሰሞ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በስካይፕ ከተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ጋ የሚያደጓቸዉን ግንኙነቶች ለመከታተል የኢንተርኔት ስለላ ፕሮግራም ልኮብኛል ባይናቸዉ።

 የግል ፋይሎቻቸዉም እሳቸዉ ባላወቁት መንገድ በኢንተርኔት መለቀቃቸዉንም ገልጸዋል። ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫም፤ ተሰደዉ ብሪታንያ ሲገቡ እንዲህ ካለዉ ክትትል ነፃ የሆኑ መስሏቸዉ እንደነበር ነዉ ያመለከቱት።

 ሎንዶን የሚገኘዉ ፕራይቬሲ ኢንተርናሽናል፤ ባዘጋጀዉ መድረክ ጉዳዩን ይፋ ሲያደርጉም የብሪታኒያ ኩባንያ በዚህ ተግባር ተሳትፎ እንደሆነ እንዲጣራላቸዉ ጠይቀዋል። ቶሮንቶ የሚገኘዉ የኢንተርኔት ተከታታይ ቡድን ሲቲዝን ላብ፤ ባደረገዉ ምርመራም ኮምፕዩተራቸዉ ብሪታንያ የሚገኘዉ ጋማ ቡድን በሚያከፋፍለዉ የኮምፒዩተር ስለላ ፕሮግራም መጠመዱን የሚያሳይ ማስረጃ አግኝቷል።

 እንደዘገባዉ ግለሰቡ በዉጭ ሃገራት ከሚገኙና ተመሳሳይ የሳይበር ጥቃት ከሚደርሳቸዉ ኢትዮጵያዉያን አንዱ ናቸዉ። የኢትዮጵያ መንግስትን በግለሰቡ የቀረበዉን አቤቱታ መሠረተ ቢስ ሲል አጣጥሏል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar