fredag 21. februar 2014

መኢአድና አንድነት በጋራ የጠሩት የባህርዳር የተቃውሞ ሰልፍ ቅስቀሳ በተሳካ ሁኔታ እየተካሄ ነው ሲሉ አስተባባሪዎች ገለጹ


ከሰልፉ አስተባባሪዎች መካከል አንዱ የሆኑት የመኢአድ ሰሜን ቀጠና አደራጅና የተቃውሞ ሰልፉ ግብረሃይል ለኢሳት እንደገለጹት የተቃውሞ ሰልፉን ለመከልከል መንግስት የተለያዩ መንገዶችን ቢጠቀምም፣ አስፈላጊውን መስዋትነት በመክፍል ቅስቀሳቸውን እያደረጉ ነው። የክልሉ መስተዳደር ዛሬ ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ፈቃድ መስጠቱንም አቶ ሽፈራው ተናግረዋል።
የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አለምነው መኮንን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ቀርበው ለማስተባበል የሞከሩት ህዝቡን ይበልጥ ማስቆጣቱንም አቶ ሽፈራው ተናግረዋል። በሌላ በኩል መንግስት በእለቱ ተመሳሳይ ተቃውሞ ለማድረግ ማሰቡ ታውቋል። ተቃዋሚዎችን የሚያውግዙ መፈክሮችን በማስጻፍ የከተማው ነዋሪ በእለቱ እንዲወጣ እና ተቃውሞውን በተቃዋሚዎች ላይ እንዲያሰማ ስራ እየሰራ መሆኑን የኢሳት የባህርዳር ወኪል ገልጻለች።
የብአዴን ሹሞች የባጃጅ መኪኖች ሾፌሮችን በመሰብሰብ በተቃውሞው ቀን ድጋፋቸውን እንዳይገልጹ ለማግባባት ሞክረዋል።
አቶ አለምነው መኮንን የአማራውን ህዝብ የሚያንቋሽሽ ዘለፋ የብአዴን ካድሬዎች በተሰባሰቡበት መድረክ ላይ መናገራቸው ይታወሳል። ም/ል ፕሬዚዳንቱ ትናንት በሰጡት መግለጫ ንግግሬ ተቆራርጦ ቀርቦብኛል በማለት ለማስተባበል ሞክረዋል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar