fredag 4. april 2014

የአዲስ አበባዉ ሰልፍ ለሚያዚያ 5 ተላለፈ !

አንድነት ፓርቲ «ህግን እያከበርን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን» በሚል ርእስ ዛሬ መጋቢት 26 ቀን 2006 ዓ.ም ይፋ ባደረገው መግለጫ «የአዲስ አበባ ከተማ ሠላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በመጋቢት 26 ቀን 2ዐዐ6 ዓም በቁጥር አ.አ ከስ/1ዐ/3ዐ.4/236 በላከልን ደብዳቤ ሠላማዊ ሠልፉን ለማድረግ በጠየቅንበት ቀን ተመሳሳይ የህዳሴ ግድብ ፕሮግራሞች ስላሉ ተለዋጭ ቀን እንድናቀርብ ጠይቆናል፡፡ በዚሁ መሠረት ለመጋቢት 28 ቀን 2ዐዐ6 ዓም ለማድረግ የያዝነውን ፕሮግራም ለማሸጋገር የህግ ግዴታ ስላለብን ለሚያዚያ 5 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ያዛወርን መሆኑን ለኢትዮጵያ ሕዝብ በአክብሮት እንገልፃለን» ሲል መጋቢት 28 ቀን ሊደረግ የታሰበውን የ እሪታ ሰልፍ ለሚያዚያ 5 መተላለፉን አሳዉቋል።
UDJ

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar