onsdag 2. april 2014

የሙስሊም መሪዎች የፍርድ ሒደት

ተከሳሾች ለፍርድ ቤቱ በሰጡት ቃል አሸባሪዎች እንዳልሆኑ፤ እስር ቤት ዉስጥ እንደተደበደቡ፤ እንደተሰቃዩና ያልተናገሩትንና ያላሉትን እንዳሉ ተደርጎ እንዲፈርሙ መርማሪዎች እንዳስፈራሯቸው ገልፀዋል
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአሸባሪነት የተከሰሱ የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ መሪዎችን የተከሳሽነት ቃል መቀበሉን ዛሬም ቀጥሎ ዉሏል።ቃሊት ያስቻለዉ የፍርድ ቤቱ አራተኛ መደበኛ ችሎት ትናንት የአንደኛ ተከሳሽ የአቡበከር አሕመድን ቃል አድምጦ ነበር።ዛሬ ደግሞ የሁለተኛ እና የሰወስተኛ ተከሳሾችን ቃል አድምጦ የተቀሩትን ተከሳሾች ቃል ለማድመጥ ለነገ-ቀጠሮ ሠጥቷል።ተከሳሾች ለፍርድ ቤቱ በሰጡት ቃል አሸባሪዎች እንዳልሆኑ፤ እስር ቤት ዉስጥ እንደተደበደቡ፤ እንደተሰቃዩና ያልተናገሩትንና ያላሉትን እንዳሉ ተደርጎ እንዲፈርሙ መርማሪዎች እንዳስፈራሯቸው ገልፀዋል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar