fredag 15. august 2014

ዓረና-መድረክ እሁድ በትግራይ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያካሂድ ነው

በመጪው እሁድ በመቀሌ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ይደረጋል። የመቀለ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ከዚህ በፊት በቂ የፖሊስ ሃይል የለንም በማለት ሰለማዊ ሰልፉ ለሌላ ቀን እንድናሸጋግረው ኣስታውቆ እንደነበር ኡእሚታወስ ነው።
የሰለማዊ ሰልፍ የሚያደርጉበትን ጎዳናዎችና የሚያርፉባቸው አደባባዮችን የሚያመላክት ደብዳቤ ትናንት 08 / 12 /2006 ዓ/ም ወደ መቐለ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ኣስገብተዋል። መድረክ ከዚህ በፊትም በኣዲስ ኣበባና በሃዋሳ ከተሞች የተሳኩ ሰለማዊ ሰልፎች ማድረጉ የሚታወስ ነው።
የአረና ቃል አቀባይ እንዳለው ከሆነ፤ ኣስተዳደሩ ያለበት የፖሊስ እጥረት በሚቀርፍ መንገድ(ዲያስፖራ ሲጠብቅ የሰነበተው በሺዎች የሚቆጠር የፌደራል ፖሊስ እያለ እንድናካሂድ የመረጥነው እጥረቱ ግምት ውስጥ ኣስገብተን ነው።) በዚህ መሰረት የሃገራችን፣ የክልላችንቻ የከተማችን ወቅታዊ ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች በማንገብ መንግስት ኣዳምጦ መፍትሄ እንዲያበጅላቸው እንጠይቃለን። እነ ኣብራሃ ደስታ፣ ኣልጋነሽ ገብሩና ሌሎች የዓረና ኣባላት፣ የመድረክ ኣባላት፣ በኣጠቃላይ በሰለማዊ መንገድ እየታገሉ ዘብጥያ የወረዱ ዜጎቻችን ፍትህ እንዲበጅላቸው ከመቐለና ኣከባቢው ህዝብና ሁነን ድምፃችን እናሰማለን ።
ነፃነታችን በእጃችን ነው…! …በማለት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar