onsdag 13. august 2014

ፖሊሶች በአበል ጉዳይ እየተወዛገቡ ነው

በዳግማዊ ሚኒልክና በሌሎችም አካባቢዎች የሚሰለጥኑ ፖሊሶች በቀን የሚታሰብላቸው ገንዘብ በቂ ባለመሆኑ
ጥያቄ አንስተዋል። ፖሊሶቹ ለቁርስና ምሳ እንዲሁም ለሻሂና ቡና 24 ብር በቀን የሚታሰብላቸው ቢሆንም፣ ገንዘቡ አይበቃንም በሚል ጥያቄ አንስተዋል።
ፖሊሶቹ  ስልጣናውን ሳያቋርጡ ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ የኮሚሽኑ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ለማግባባት እየሞከሩ ነው።
በዳግማዊ ሚኒሊክ ት/ቤት ውስጥ ካለፉት 2 ሳምንታት ጀምሮ ከ500 በላይ ፖሊሶች እየሰለጡ ነው። ስልጣናው መጪውን ምርጫ ታሳቢ አድርጎ የሚሰጥ
ነው። በኮልፌ በነበረው  ስልጠና ላይ ፖሊሶች ከመብት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንስተው እንደነበር መዘገባችን ይታወቃል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar