torsdag 14. august 2014

እነ ወይንሸት ሞላ በዋስ እንዲፈቱ በድጋሚ ታዘዘ

ያለአግባብ ታስረው የነበሩት የሰማያዊ ፓርቲዋ ወይንሸት ሞላና ፎቶ አንሺ ጋዜጠኛዋ አዚዛ መሃመድ ከሁለት ሳምንታት በፊት በአንዋር መስጊድ ይካሄድ በነበረው የጁምአ በአል ላይ ተገኝተው ነበር። የፖሊስ እና ደህንነት ሃይሎች ሰላማዊውን ሰው ሲደበድቡ እና ሲያስሩ፤ እነ ወይንሸት ሞላም በስፍራው በመገኘታቸው ብቻ ከፍተኛ ድብደባ ደርሶባቸው ታስረዋል። በተለይም ወይንሸት ሞላ እጇ እስኪሰበር ድረስ ነበር የተደበደበችው። ባለፈው ሳምንት የዋለው የልደታ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለቱም እንዲፈቱ ቢያዝም፤ ፖሊስ ወዲያው ጉዳዩን ሰበር ችሎት ወስዶ ዋሳቸውን አሳግዶባቸው እንደነበር ይታወሳል።
ወይንሸት ሞላ
ወይንሸት ሞላ (የሰማያዊ ፓርቲ ሴት ወጣቶች ሃላፊ)

አዚዛ መሃመድ - የአዲስ ጉዳይ መጽሄት ፎቶ አንሺ።
አዚዛ መሃመድ – የአዲስ ጉዳይ መጽሄት ፎቶ አንሺ።
በዛሬው ቀን የዋለው ችሎት ወይንሸት ሞላ፣ አዚዛ እና ኢብራሂም አብዱልሰላም በ5ሺህ ብር የመታወቂያ ዋስ እንዲፈቱ ውሳኔ ሰጥቷል። እንደከዚህ ቀደሙ መልሰው ካላሰሯቸው በቀር ሶስቱም በቅርቡ ከ እስር ይወጣሉ ተብሎ ይታወቃል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar