mandag 25. august 2014

ኦህዴድ በየደረጃው ያሉ አመራሪዎችን ለአስቸኳይ ስብሰባ ጠራ

በሁሉም የኦሮምያ ክልሎች  በሚገኙ ዞኖች ውስጥ የሚገኙ አስተዳዳሪዎች፣ የግብርና ዋና እና ምክትል
ሃላፊዎች፣ የሴቶች ጽ/ቤት ፣ መሬት ጥበቃ ፣ ሲቪል ሰርቪስ እና መልካም አስተዳደር ፣ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፣ ውሃና ማእድን፣ ገጠር መንገድ ፣ ጥቃቅንና
አነስተኛ ጽ/ቤት ፣ ገንዘብና ኢኮኖሚ ፣  ትምህርት/ጽ/ቤት፣ እና  የወጣቶችና ስፖርት ሃላፊዎች ከነገ ጀምሮ ለአስቸኳይ ስብሰባ እንዲከቱ ተደርጓል። አስቸኳይ
ስበሰባው ለምን እንዳስፈለገ ባይታወቅም፣ ሰሞኑን ኢህአዴግ እያደረገ ካለው ግምገማ እንዲሁም በድርጅቱ ውስጥ የሚታዩትን ችግሮች ከመገምገም ጋር ሊያያዝ
እንደሚችል ምንጮች ጠቁመዋል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar