søndag 21. september 2014

የኢህአዴግ አምባሳደር በስዊዲን ወየንሽት ታደሰ የእንቁላል ድብደባ በከፍተኛ ሁኔታ ደረሰባት።

በስዊዲን የሚገኙ ኢትዮጵያኖች ከዚህ በሆላ እንደድሮው በውጪ እየወጡ መዝናናት የለም በማለት አምባሳደሯን እንቁላል በመወርወር ከፍተኛ የሆነ ውርደት እንድተከናነብ አድርገዋል። አብረዋት የነበሩ የወያኔ ጠባቂዎችም ራሳቸውን ከድብድባው ለማምለጥ ሲሉ ጥለዋት ሄደዋል። የስዊድን ፖሊሶች በርካታ የፖሊስ መኪናዎችን በማምጣት ጸጥታውን ለመቆጣጠር የቻሉ ሲሆን ከረጅም እግታ በሆላ በፖሊሶች እርዳታ ከመኪናዋ ወጥታ ለመሄደ ችላለች።
የኢህአዴግ አምባሳደር በስዊዲን ወይንሽት ታደሰ የእንቁላል ድብደባ በከፍተኛ ሁኔታ ደረሰባት።
እንቁላል አትጨርሱ ዛሬ የባንዳዎች እና የነነዋይ ውርደት በእንቁላል ቢጫ እናድረጋቸዋለን እና እሶ ላይ ብቻ አትጨርሱ፣ መኪናው የእንቁላል ጌጥ በዛበት የሚል አስቂኝ ክስተቶችም ነበሩበት።
በውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያኖች በተጠናከረ መልኩ የወያኔን ባለስልጣናት በሄዱበት የማዋረድና እጃቸው ደም የተበከለ መሆኑን በተደጋጋሚ እየተነገራቸው ሲሆን በቅርቡ በተመሳሳይ ሬድዋን ሁሴን በዋሽንግተን ዲዲ የደረሰበት ውርደት ይታወሳል።
በአሁኑ ሰአት በርካታ የወያኔ ባለስልጣኖች ወደ ውጪ መጓዝን እንደማይመርጡ የደረሰን ሪፖርት ያመላክታል።
በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳና እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar