tirsdag 12. mars 2013

ፎቶ ጋዜጠኛ ቢንያም መንገሻ ተሰደደ


በተለያዩ ፎቶግራፎቹ ከፍተኛ እውቅና ያተረፈው ጋዜጠኛ ቢንያም መንገሻ አገሩን ጥሎ ለመሰደድ የተገደደው በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አገዛዝ አገሪቱን ሙሉ በሙሉ እያወደማት መሆኑን በመገንዘብ፣ የራሱን አስተዋጽኦ ለማድረግ ነው።

ጋዜጠኛ ቢንያም ከኢሳት ጋር ባደረገው ሰፊ ቃለምልልስ በስልጣን ላይ ያለው ሀይል ኢትዮጵያ በመኖርና ባለመኖር መካከል ከትቷታል።

በመንግስት የተበላሸ ፖሊሲ የተነሳ ኢትዮጵያ በፍጥነት ወደ ምደረ በዳነት እየተቀየረች መሆኑን በፎቶግራፍ በማስደገፍ ለኢሳት ገልጿል።

ፎቶ ጋዜጠኛ ቢንያም መንገሻ በሪፖርተር ጋዜጣ እና በአቢ ዊክሊ መጽሄት ሲሰራ ከቆየ በሁዋላ፣ ያራሱን ግላመር ፎቶ ስቱዲዮ በማቋቋም ፎቶ ኢግዢቢሺኖችን ማሳየቱን፣ በዚህም ስራው፣ የአገሪቱን መልካም ገጽታ አበላሽቷል በሚል በደህንነት ሀይሎች ሲዋከብ እንደነበር ገልጿል።

ከጋዜጠኛ ቢንያም መንገሻ ጋር የተደረገው ቃለምልልስ በቅርቡ ይቀርባል።
ሰሜንና ደቡብ ኮሪያ ተፋጠዋል

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar