lørdag 2. mars 2013

ሰው ሊኖር ሰው ሞቷል

ሰው ሊኖር ሰው ሞቷል»ያኔ
ይኸው በእኛ ዘመን ዛሬ 117ኛው የአድዋ ድል በዓል የሚከበርበት እለት ሆኖ ተጽፏል፡፡ ታሪክ ለማውራት እንጂ ለመስራት ያልታደልን ዘመነኞች፡፡ያኔ ያኔ ነጻነታችን ሊጋፋ፣ ክብራችንን ሊገፍ፣ የመጣው ባዕድ ነበርና እናት አባቶቻችን ለእኛ ለልጆቻቸው ባርነትን ላማውረስ ሲሉ፣ ስለነጻነታችን ሲሉ፣ ጠላትን ተጋፈጡልን፣ ህይወታቸውን ከፈሉልን፡፡የእኔ የምንግዜም ምርጥ ተቀኚ እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) እነርሱን በአመሰገነችበት «አድዋ» ሙዚቃዋ እንደተቀኘችውም ያኔ «ሰው ሊኖር ሰው ሞቷል» አሁንስ?
እንዲህም አስባለሁ፡፡ አሁን እኚያ የሞቱልን የቀደሙቱ ወገኖቻችን እንደው ለአንድ አፍታ ከመቃብራቸው ወጥተው «እኛ የሞትንላት ኢትዮጵያን የት አለች? ያወረስናችሁ ነጻነትስ ወዴት አለ? ልጆቻችን ሆይ!!የኢትዮጵያዊነት ከፍታ ከምን ደረሰ ? የእናንተ ዘመን መዘመን ምን በጃችሁ? ጠግባችሁ ማደርስ ቻላችሁ?» ብለው ቢጠይቁንስ ምን ብለን እንመልስ ይሆን? እኔስ በኩራትና በድፍረት የምመልሰው ነገር የለኝም ፡፡የእነርሱን የመስዋዕትነትና የድል ታሪክ ግን ለእኔም ዘመን እመኘዋለሁ፡፡ሁሌም አንዲት ኢትዮጵያ!!!
«ሰው ሊኖር ሰው ሞቷል»ያኔ
ይኸው በእኛ ዘመን ዛሬ 117ኛው የአድዋ ድል በዓል የሚከበርበት እለት ሆኖ ተጽፏል፡፡ ታሪክ ለማውራት እንጂ ለመስራት ያልታደልን ዘመነኞች፡፡ያኔ ያኔ  ነጻነታችን ሊጋፋ፣ ክብራችንን ሊገፍ፣ የመጣው ባዕድ ነበርና እናት አባቶቻችን ለእኛ ለልጆቻቸው ባርነትን ላማውረስ ሲሉ፣ ስለነጻነታችን ሲሉ፣ ጠላትን ተጋፈጡልን፣ ህይወታቸውን ከፈሉልን፡፡የእኔ የምንግዜም ምርጥ ተቀኚ እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) እነርሱን በአመሰገነችበት «አድዋ» ሙዚቃዋ እንደተቀኘችውም ያኔ «ሰው ሊኖር ሰው ሞቷል» አሁንስ? 
 እንዲህም አስባለሁ፡፡ አሁን እኚያ  የሞቱልን የቀደሙቱ ወገኖቻችን እንደው ለአንድ አፍታ ከመቃብራቸው ወጥተው «እኛ የሞትንላት ኢትዮጵያን የት አለች? ያወረስናችሁ ነጻነትስ ወዴት አለ? ልጆቻችን ሆይ!!የኢትዮጵያዊነት ከፍታ ከምን ደረሰ ? የእናንተ ዘመን መዘመን ምን በጃችሁ? ጠግባችሁ ማደርስ ቻላችሁ?» ብለው ቢጠይቁንስ ምን ብለን እንመልስ ይሆን? እኔስ በኩራትና በድፍረት የምመልሰው ነገር የለኝም ፡፡የእነርሱን የመስዋዕትነትና የድል ታሪክ ግን ለእኔም ዘመን እመኘዋለሁ፡፡ሁሌም አንዲት ኢትዮጵያ!!!

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar