søndag 3. mars 2013

በኢትዮጵያ “የጥበብን ስራ እንኳ በነጻነት ማካሄድ አይቻልም” ሲሉ አንድ የጀርመን ፋውንዴሽን ዳይሬክተር ተናገሩ



ከኢትዮጵያ ለቅቆ የወጣው የጀርመን ሄንሪክ ቦል ፋውንዴሽን የኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ፓትሪክ በርግ ድርጅታቸው ከኢትዮጵያ ስለለቀቀበት ምክንያት ለብሉበርጉ ዊሊያምስ ዳቪሰን ሲናገሩ “በኢትዮጵያ የጥበብ ስራ እንኳን በአሁኑ ጊዜ በጥርጣሬ የሚታይ ነው፣ ከመብት ጋር የተያያዘውን ስራችሁን አቁሙ በመባላችን ስራችንን ለቀን ወጥተናል” ብለዋል።

የሲቪክ ሶሳይቲና ቻርቲ ህግ የሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ውርስ መሆኑን የገለጠው ብሉምበርግ፣ ህጉ ከመንግስት የተለየ ሃሳብ ያላቸውን ተቃዋሚዎች እና ድርጅቶች ለመቆጣጠር የወጣ መሆኑን አምነስቲ ኢንተርናሽናልን በመጥቀስ ዘግቧል።

የሂውማን ራይትስ ወች የአፍሪካ ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል በቀለ ፣ መንግስት ያወጣው የሲቪክ ሶሳይቲና ቻሪቲ ህግ የአለማቀፍ ማህበረሰቡን ለማግለል ታስቦ የተረቀቀ አለመሆኑን ገልጸው ፣ ዋና ግቡ በአገር ውስጥ ካለው ፖለቲካ እና ሲቪክ ሶሳይቲ ስራ ጋር የተያያዘ ነው ብለዋል።

“ህጉ ለ1997 ምርጫ መልስ ነው። ለመራጮች የተሰጠው ትምህርት ከፍተኛ መራጮች እንዲገኙ ማድረጉ፣ ሲቪክ ሶሳይቲው ምርጫውን መታዘቡና ልዩነቶችን መሸምገሉ፣ በመንግስት በኩል ሲቪክ ሶሳይቲው የፖለቲካ ስራ እየሰራ ነው የሚል መልእክት ማስተላለፉን” ገልጸዋል።

የመንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ ህጉ በሙስና የተዘፈቁ የሲቪክ ድርጅቶችን ለመቆጣጠር ተብሎ የተረቀቀ መሆኑን በመግለጽ፣ የመንግስትን አቋም አንጸባርቀዋል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar