fredag 13. september 2013

ርእዮት አለሙ ምግብ ካቆመች 4ኛ ቀናትን ደፈነች

እውቋ የብእር ሰው፣ የነጻነት ታጋይ፣ የዩኒስኮና የኢንተርናሽናል ውሜንስ  ሚዲያ ፋውንዴሽን አሸናፊ ጸሀፊና መምህርት ርእዮት አለሙ ዛሬም በረሀብ አድማው ገፍታበታለች። እህቷ እስከዳር አለሙ እንደገለጸችው ዛሬ እርሷና የርእዮት እጮኛ የሆነው ስለሺ ሀጎስ ወደ ቃሊቲ እስር ቤት ቢሄዱም እንዳይገቡ ተከልክለዋል።
እጮኛዋ ስለሺ ለሰአታት ታግቶ በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች መደብደቡንም እስከዳር ተናግራለች  ርእዮት ከእናት፣ አበቷና የንስሀ አባታ በስተቀር ሌላ ሰው እንዳይጠይቃት በመደረጓ የረሀብ አድማውን መጀመሩዋ ይታወቃል።
በአለም ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በርእዮት ላይ የሚደርሰውን የመብት አፈና እየተቃወሙ ነው።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar