torsdag 1. mai 2014

በጎንደር ከቤት ማፍረስ ጋር በተያያዘ በተነሳ ረብሻ 3 ሰዎች ተገደሉ

ዛሬ ጧት ገንፎ ቁጭ በሚባለው አካባቢ በህገወጥ መንገድ ተሰርተዋል የተባሉ ቤቶችን ለማፍረስ ቀለም የመቀባት ስራ በተጀመረበት ወቅት ረብሻ መቀስቀሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
የፌደራል ፖሊስ በወሰደው የሃይል እርምጃ አንድ ሰው ሲገደል የአካባቢው ነዋሪ በወሰደው የአጸፋ እርምጃ ደግሞ አንድ ፖሊስና አንድ ታጣቂ ሚሊሺያ ተገድለዋል።
የፌደራል ፖሊሶች በርካታ ወጣቶችን ይዘው ያሰሩ ሲሆን፣ አንዳንዶች አካባቢውን ጥለው መሸሻቸው ታውቋል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar